TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ወ/ሮ ሙፈሪያት ከሚል⬇️

በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ ሂደት ከመደገፍና ከማሳደግ ውጪ ሌላ #አማራጭ እንደሌለ የደኢህዴን ሊቀ መንበር በመሆን በድጋሚ የተመረጡት ወይዘሮ #ሙፈሪያት_ካሚል ገለፁ።

ሊቀ መንበሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል 10ኛው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) ድርጅታዊ ጉባዔ #መጠናቀቅን ተከትሎ ለጉባኤተኛው የማጠቃለያ መልእክት አስተላልፈዋል።

ወይዘሮ ሙፈሪያት በማጠቃለያ ንግግራቸው፥ ሀገሪቱ በአሁኑ ወቅት በለውጥ ሂደት ላይ መሆኗን ገልፀው፤ የደኢህዴን አባላት፣ አመራሮች እና ጉባዔተኛው ለውጡ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መስራት አንዳለባቸው ገልፀዋል።

ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ ለውጥ #ለማደናቀፍ ሌት ተቀን የሚሰሩ ሀይሎች እንዳሉ ሊቀመንበሯ ገልፀዋል።

እነዚህ ሀይሎች 10ኛው የደኢህዴን ጉባዔ እንዳይሳካም ሲንቀሳቀሱ ነበር ያሉት ወይዘሮ ሙፈሪያት፤ ከሀዋሳ ውጪ በህዝቦች መካከል #ግጭት ለመፍጠር ገንዘብ ተመድቦላቸው #ሲንቀሳቀሱ እንደነበረ ከክልሉ የፀጥታ ሀይሎች ጋር በተሰራ ስራ ለማወቅ መቻሉን አንስተዋል።

የደኢህዴን አባላት፣ አመራሮች እና ጉባዔተኛው ይህንን በመገንዘብ እነዚህን የጥፋት ሀይሎች በንቃት መጠበቅና ማጋለጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለውን ሀገራዊ የለውጥ ሂደት ከመደገፍና ካማሳደግ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም ያሉት ሊቀ መንበሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት፥ ከዚህ ውጨ ያለው አማራጭ #የጥፋት አማራጭ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

ስለዚህ የለውጥ ጉዞውን በማሳከት ሂደት የደኢህዴን አባላት፣ አመራሮች እና የጉባኤተኛው ሚና አጅግ የላቀ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

ከነገ ጀምሮ #በሀዋሳ ከተማ የሚካሄደው 11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ እንዲሁም የተጀመረውን የህዳሴ ጉዞ ከዳር ለማድረስ የሚደረገውን ርብርብ መቀጠል ይኖርብናል ሲሉም ተናግረዋል።

በኢህአዴግ ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ የደኢህዴን ጉባዔተኞች ልክ በደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ ላይ ያደረጉትን የነቃ ተሳትፎ፣ ዴሞክራሲያዊ ሂደትና ሰላማዊ ሁኔታን እንዲያስቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሊቀ መንበሯ ወይዘሮ ሙፈሪያት አክለውም፥ 10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ በዚህ መልኩ የተሳካ ሆኖ በመጠናቀቁም እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን ብለዋል።

ጉባዔው የተሳካ እንዲሆን የሀዋሳ ከተማ እና የሲዳማ ዞን እንዲሁም የልግ ባለሀብቶች ላደረጉልት አቀባበል እንዲሁም የኢህአዴግ ጉባዔን ለማስተናገድ እያደረጉ ላለው ዝግጅት ለአመራሩ እና ለህዝቦች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ - ሀዋሳ⬇️

11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ የማጠቃለያ ስነ ስርዓት #በሀዋሳ ከተማ በዛሬው ዕለት ተከናውኗል።

በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት የድርጅቱ ሊቀመንበር ዶክተር አብይ አህመድ፥ የኢትዮጵያ ህዝብ የሀገሪቱን #ሰላም ለማስጠቅ ከመንግስት ጐን እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

ሊቀመንበሩ በንግግራቸው፥ 11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ በሀገሪቱ ውስጥ የነበሩ ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች የማያሰሩ ከሆነ እንዲሻሻሉ አቅጣጫ እንደተቀመጠ አስታውቀዋል።

#የምርጫ_ኮሚሽንና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በአመራር፣ በቴክኖሎጂና በተለያዩ መንገዶች እራሳቸውን #እንዲያሻሽሉ ጉባዔው መወሰኑንም ተናግረዋል።

በሀገሪቱ በቀጣይ የሚካሄደው ምርጫ ነጻ፣ ፍትሃዊና ገለልተኛ እንዲሆን በሀዋሳ ለሶስት ቀናት የተካሄደው ጉባዔ ውሳኔ ማሳለፉን ነው ሊቀመንበሩ ያስታወቁት።

ሀገሪቱን እያስተዳደረ ያለው ፓርቲ በአዲስ ጉልበት አዲስ ሀይል #በወጣቱ እየተደራጀ መሆኑን የገለፁት ዶክተር አብይ፥ #ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ከወዲሁ በመሰባሰብ ጠንካራ #አማራጭ ፓርቲ መሆን እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

ሊቀመንበሩ፥ ፓርቲያቸው ለተፎካካሪ ፓርቲዎች መሻሻል አስፈላጊውን ድጋፍ ለመስጠት መዘጋጀቱን የገለፁ ሲሆን፥ ማሸነፍ ብቻ ሳይሆን መሸነፍም እንዳለ በመገንዘብ መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

ተፎካካሪ ፓርቲዎች ኢትዮጵያን ለማገልገልና የተሻለ ለመሆን በአዲስ አመራር፣ በወጣቶች እና በምሁራን እራሳቸውን ማደረጃት እንዳለባቸውም ነው የተናገሩት።

ለኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት እውነተኛ፣ ትክክለኛና ጠቃሚ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ የሚያደርሱ መገናኛ ብዙሃን ናቸው ያሉት ሊቀመንበሩ፥ መገናኛ ብዙሃን #የኢትዮጵያዊ ማንነትን ባልጣሰ መልኩ ሊንቀሳቀሱ ይገባል ብለዋል።

ጉባዔው ለግብርና፣ መስኖ ልማት እና ኢንቨስትመንት ትኩረት በመስጠት የስራ አጥነትነትን ለመቀነስ በልዩ ሁኔታ እንዲሰራ አቅጣጫ እንዳስቀመጠም ተናግረዋል።

የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ቱሪዝም መሆኑን የተናገሩት ዶክተር አብይ፥ ኢትዮጵያውያን ከዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን እራሳቸውን በተለያዩ መንገዶች ማዘጋጀት እንደሚገባቸውና አፍሪካውያን ወንድሞቻቸውን ለመቀበል እንዲዘጋጁ አሳስበዋል።

የሀገሪቱ ከተሞች ያደጉና ድህነትን የቀነሱ እንዲሆኑ በቀጣይ በትኩረት ለመስራት አቅጣጫ እንተጠቀመጠ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።

በተለይ የአፍሪካ መዲና የሆነችውን አዲስ አበባ ፅዱና ውብ ለማድረግ እንደሚሰራ የተናገሩ ሲሆን፥ ለዚህም የከተማዋ ወጣቶችና ነዋሪዎች ከመንግስት ጎን እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢህአዴግ ውስጣዊ አንድነት በማጠናከር #የኢትዮጵያውያን አንድነት ለመጠበቅ ይሰራልም ብለዋል።

ብልሹ አሰራር ከባህላችን ጋር የሚቀራን ነው ያሉት ሊቀመንበሩ፥ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሚከፈለው ልክ ሳይሆን ከሚከፈለው በላይ መስራት እንደሚገባው ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የመን አላርም ትሁነን!

•ከ70 ሺህ በላይ ንፁሃን ህይወታቸውን አጥተዋል!
•ከ11 ሺህ በላይ ዜጎች አካላቸው ጎድሏል!
•24 ሚሊዮን ዜጎች አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል!
•ባለፉት 3 ዓመታት ውስጥ ብቻ 85 ሺህ እድሜያቸው ከ5 ዐመት በታች የሆኑ ህፃናት በምግብ እጥረት ሞተዋል!
•በርካታ ሚሊዮን ዜጎች ቤታቸውን ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል!

ብልቂሳ አብደላ ከ20 ዓመታት በላይ በየመን ነዋሪ ናት ይህንን ብላለች፦ "ወላሂ! የጦርነት ጥሩ ነገር የለም፤ የመንን ያየ... ሰላም የሆነውን ሀገር ባያደፈርሱ ጥሩ ነው። ...ኢትዮጵያ ችግር አለ ሲባል የመንን፣ ሶሪያን፣ ኢራቅን አላዩም ወይ...የመን እንኳን አንድ ቋንቋ፤ አንድ ሃይማኖት ነው፤ ይሄ ደግሞ የተለያየ ስላለ ከጀመረ የሚያቆም አይመስለኝም"

የመን ለምን እንዲሆነች??
•አለመደማመጥ
•ምክንያታዊ ሆኖ አለማሰብ

#የመናውያን መነጋገርና መደራደር የሚለውን #አማራጭ ባለመተግበራቸው ለዚህ ችግር ተጋልጠዋል። ጦርነት ሩቅ አይደለም፤ በፖለቲካና በሃይማኖት መካረሩ መዳረሻው ግልፅ ነው👉ጦ ር ነ ት!

#TIKVAH_ETHIOPIA

Via #SRTA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbaba

ዛሬ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ይዘጋሉ።

የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል መንገዶች የሚዘጉት ለ " ፀጥታ ስራ ሲባል " መሆኑን ገልጾ ለተሽከርካሪም ሆነ ለእግረኞች ዝግ እንደሚደረጉ ነው ያመለከተው።

የጋራ ግብረ ሃይሉ ከቀናት በኋላ በአ/አ በሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለሚከናወነው #የአጀብ እና #የፀጥታ ስራዎች ምክንያት በማድረግ #ሁሉም_የፀጥታ_አካላት_የሚሳተፉበት ወታደራዊ የተግባር ልምምድ እንደሚከናወን አሳውቋል።

ለዚሁ ሲባል የሚከተሉት መንገዶች ለተሽከርካሪ እና ለእግረኞች ዝግ ይደረጋሉ ፦

🚘 ከጎተራ መሳለጫ ወይም ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ጎተራ መሳለጫ ጋር፤

🚖 ከቂርቆስ ታቦት ማደሪያ ወደ ለገሀር የሚወስደው ቂርቆስ ታቦት ማደሪያ መስቀለኛ  ላይ ፤

🚘 ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ ለሚመጡ ቡልጋሪያ ማዞሪያ፤

🚖 ከሳር ቤት በአፍሪካ ህብረት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ለሚመጡ ሳር ቤት አደባባይ፤

🚘 ከካርል አደባባይ በልደታ ፀበል ወደ ከፍተኛ ፍ/ቤት  ለሚመጡ ካርል አደባባይ፤

🚖 ከጦር ሃይሎች ወደ ሜክሲኮ አደባባይ አዋሽ ወይን ጠጅ ፋብሪካ፤

🚘 ከአብነት ወደ ጌጃ ሰፈር አብነት አደባባይ፤

🚖 ከሞላ ማሩ ወደ አብነት ፖሊስ ጣቢያ ለሚመጡ ሞላማሩ መስቀለኛ ፤

🚘 ከበርበሬ በረንዳ ወደ ቀድሞ 5ኛ ፖሊስ ጣቢያ  ለሚመጡ በርበሬ በረንዳ፤

🚖 ከተ/ሃይማኖት ወደ ጎማ ቁጠባ ተ/ሃይማኖት አደባባይ፤

🚘 ከቴዎድሮስ አደባባይ በቸርችል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ የሚሄደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ዝግ የተደረገ ሲሆን ከየትኛውም አቅጣጫ ወደ አራት ኪሎ መሄድ የተከለከለ ነው፡፡ 

🚖 ከሽሮ ሜዳ ወደ 6 ኪሎ እና ወደ 4ኪሎ የሚያስኬደው መንገድ  ሽሮ ሜዳ ጋር የሚዘጋ ሲሆን ከ4 ኪሎ ወደ ቤተ መንግስት የሚወስደው መንገድ ዝግ ተደርጓል፡፡ 

🚘 ከቀበና ወደ 4ኪሎ ቀበና አደባባይ ፤

🚖 ከጀርመን አደባባይ እና ከሲግናል አካባቢ ወደ 4 ኪሎ ጥይት ቤት ለሚመጡ ጀርመን አደባባይ ፤

🚘 ከካዛንቺስ መናህሪያ ወደ 4ኪሎ እና ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሴቶች አደባባይ፤

🚖 ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ ወሎ ሰፈር ፤

🚘 ከመገናኛ ወደ መስቀል አደበባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል መስቀለኛ ፤

🚖 ከቅዱስ መርቆሪዮስ አደባባይ ወደ መስቀል ፍላወር ቅዱስ መርቆሪዮስ አደባባይ፤

🚘 ከአፍንጮ በር ወደ 6 ኪሎ አፍንጮ በር፤

🚖 ከፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ ወደ 6 ኪሎ የሚያመጣው 6 ኪሎ ዝግ ይሆናል፤

🚘 ከሚኒሊክ ሆስፒታል ወደ 6 ኪሎ የሚያመጣው መንገድ 6 ኪሎ ቶታል ጋር ዝግ የሚደረግ ሲሆን በተጨማሪም ወደ 4 ኪሎ እና በቅርበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚያመጡ አቋራጭ መንገዶች ዝግ የሚደረጉ ይሆናል ተብሏል።

በተጨማሪም #ለእግረኛ ተጠቃሚዎች፦

🚶መስቀል አደባባይ 4ተኛ ክፍለ ጦር ወይም ጥላሁን አደባባይ ዙርያ፣
🚶‍♂ኦሎምፒያ ዙርያ፣
🚶‍♂ከኡራኤል ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ ከቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከሀራምቤ ወደ መሰቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከለገሀር ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከባምቢስ ወደ መስቀል አደባባይ፣
🚶‍♂ከትምህርት ሚኒስቴር በአራት ኪሎ ብሔራዊ ቤተ መንግስትና ወደ ቦሌ እንዲሁም ከቀበና ወደ አራት ኪሎ የሚወስደው መንገድ ዝግ መሆኑ ተነግሯል።

ዝግ ሆኖ የሚቆየው ከለሊቱ 11፡ 00 እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ሲሆን ህብረተሰቡ #አማራጭ_መንገዶችን እንዲጠቀም ጥሪ ተላልፏል።

(የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF " ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " - ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል። የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በዛሬው የምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ወቅት ፤ " የሰላም ስምምነቱ ቀሪ ጉዳዮች ቢኖሩም ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ…
#TPLF

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት / ከሽብርተኛ ድርጅትነት በተሰረዘበት የዛሬው የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ልዩ ስብሰባ ላይ 280 የፓርላማ አባላት ተገኝተው ነበር።

ከተገኙት የፓርላማ አባላት መካከል 61 የፓርላማ አባላት ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት መሰረዙን #ተቃውመው ድምፅ ሰጥተዋል።

5 የፓርላማ አባላት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል።

በዚህም #በአብላጫ_ድምፅ ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት ይነሳ የሚለው የውሳኔ ሃሳብ ፀድቋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔውን ተከትሎ ባሰራጨው መረጃ ፤ " በህወሓትና በፌደራል መንግስት በኘሪቶሪያ የተደረገውን ሥምምነት ለማጽናት ህወሐትን ከሽብርተኝነት ስያሜ ማንሳት #አማራጭ_የሌለው ጉዳይ መሆኑን የውሳኔ ሃሳቡ በቀረበበት ወቅት ተነስቷል " ብሏል።

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

ነገ በአዲስ አበባ የተወሰኑ መንገዶች #ይዘጋሉ

" የሚጠብቁንን ጀግኖች እናክብር " በሚል መሪ ቃል በዓለም ለ24ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ2ኛ ጊዜ የሚከበረውን ' የእሳት አደጋ ሰራተኞች ቀን ' ክብረ በዓልን አስመልክቶ በመስቀል አደባባይ ዙሪያ ለተወሰነ ሰዓት  መንገድ ዝግ ይደረጋል ተብሏል።

በመስቀል አደባባይ ዙሪያ መንገዶች ዝግ የሚደረጉት ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ መሆኑ ተገልጿል።

የሚዘጉ መንገዶች ፦

- ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን ፤

- ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ፤

- ከላንቻ ወደ መስቀል አደባባይ አራተኛ ክፍለ ጦር ዝግ የሚደረግ ሲሆን #ለከባድ ተሸከርካሪዎች ጥላሁን አደባባይ ጋር ዝግ የሚደረግ ይሆናል።

- ከከፍተኛው ፍ/ቤት ፣ በለገሃር ወደ  መስቀል አደባባይ ለገሐር መብራት ፤

- ከጎማ ቁጠባ በብሔራዊ ቴአትር ወደ  መስቀል አደባባይ ቴሌ መስቀለኛ ወይም ክቡ ባንክ፤

- ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሐራምቤ ሆቴል መስቀለኛ ፤

- ከ4 ኪሎ በውጭ ጉዳይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት መስቀለኛ ላይ ፤ ከማለዳው 12:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ 5:00 ሠዓት ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች ሌሎች #አማራጭ_መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia