TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Haramaya University--#StopHateSpeech👆

Dubbii(Haasaan) jibbinsaa/HATE SPEECH/ jechuun #ilaalcha namoota dhunfaa, ykn garee Amantii, Sabaa, Sanyummaa ykn Haala qaama irratti Hundaa'uun dubbi/haasaa taasiifamu ykn Bu'aa miidiiyaa hawasaatii.

Kunis walitti deeddeebinsaa jechootaa namoota dhunfaa lama gidduutti gaggeefamuu jalqabee hanga Midiyaalee sab-qunnamtii gurguddoo irrattis hanga tamsasaahutti gahuu danda'a.
Kanaaf #haasaa(dubbii) #jibbinsaa_irraa_of_haa_qusannuu!!
.
.
.
እጅግ በጣም የምንወዳችሁ እና የምናከብራችሁ የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና የተቋሙ አመራሮች ነገ እና ከነገ በስቲያ በዋናው ግቢ ተገናኝተን የጥላቻ ንግግርን እናወግዛለን!!

√ጅማ ዩኒቨርሲቲ
√ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
√ወ/ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
√አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ
√ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
√ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
√ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ሀገራዊ አላማ በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ይገናኛሉ!!

እኛ #ኢትዮጵያን በፍቅር፤ በመከባበር በአንድነት እንገነባታለን!! TIKVAH-ETH /ወጣቶቻችን የነገ የሀገሪቱ ተስፋ ናቸው!!/

#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ውብ ሀገሬ!

ውብ ሀገሬ፤ ውብ ሀገሬ፣ውብ ሀገሬ
ባንቺ እኮ ነው፤ መከበሬ፤ መከበሬ
.
.
እናት አባት ቢሞት በሀገር #ይለቀሳል
እህት ወንድም ቢሞት በሀገር ይለቀሳል
#ሀገር የሞተ እንደሁ ወዴት ይደረሳል?

▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️

#ኢትዮጵያን መውደድ ማለት፦ ህዝቦቿን፣ የህዝቦቿን ባህል፣ ቋንቋ፣ እምነት እና ስርዓት #መውደድ እና #ማክበር ማለት ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጅግጅጋ

"#የሁላችንም የሆነች #ኢትዮጵያን ለመፍጠር ቀን ከሌት እንሰራለን" የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሽመልስ_አብዲሳ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኩራት ቀንዎ ነፃ ቡና እንሆ!

ቶሞካዎች ተመስግናችኃል!


አዲስ አበባ መስቀል ፍላወር የሚገኘው "ቶሞካ ቡና" የኩራት ቀንን ምክንያት በማድረግ ደንበኞቹን በነጻ ቡና እያጠጣ ነው፤ በቡናችሁ ኩሩ እያለ ይገኛል☕️

በነገራች ላይ...የሀገራችን ቡና #ኢትዮጵያን በዓለም ላይ እንድትታወቅ በማድረግ ትልቁን ድርሻ ይይዛል!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንደምን አረፈዳችሁ?

በ10,000 ሺህ የሚቆጠሩ በ @tikvahethiopiaBot የተከማቹ መልዕክቶችን እየተመለከትን ነበር። ከመላው ሀገሪቱ ክፍል ማለት ይቻላል።

ትላንት ምሽት 'ሻይቅጠል በጥብጣችሁ ጠጡ፣ የሻይቅጠል ፈልጋችሁ በስኴር አድርጋችሁ ጠጡ' ለኮሮና መድሃኒት ነው ተብለን ነበር የሚሉ መልዕክቶችን ተመልክተናል።

እውነቱ ግን ብቸኛ የአሁኑ መፍትሄ የጤና ባለሞያዎችን ምክር መስማት ብቻ ነው። በተለያየ መልኩ በሚደርሳችሁ መልዕክቶች ሁሉ የምትረበሹ ከሆነ ይህን የኮሮና ቫይረስ መቆጣጠር ፍፁም አዳጋች ነው የሚሆነው።

#ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት የሚደረጉ ጥረቶች ቢደነቁም እውነታው ግን ኮሮና ቫይረስ መድሃኒት የሌለው ገዳይ ወረርሽኝ መሆኑ ነው። መድሃኒት ቢገኝለት የሁላችን ደስታ ነው ፤ ግን መድሃኒት የለውም ፤ አልተገኘለትም! ከበሽታው የምንተርፈው በጤና ባለሞያዎች ምክር ብቻ ነው።

መዘናጋት ከምንነግራችሁ በላይ ትልቅ ዋጋ ያስከፍላልና ጥንቃቄ ይደረግ። ባልተሟላ የህክምና ቁሳቁስ ፣ እራሳቸውን አደጋ ላይ ጥለው የእኛን ህይወት ለመታደግ ዝግጁ በሆኑት የጤና ባለሞያዎቻችን ላይ ስቃያቸውን እንዳናበዛ የሚሉትን እንስማ።

መልካም ቀን!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UNSC

ዛሬ የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ይመክራል።

ስብሰባው ላይ ለመካፈል የኢትዮጵያ ዉኃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚንስትር ዶ/ር ኢ/ር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ ወደ ኒውዮርክ ማቅናታቸውን አል አል ዐይን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ የፀጥታው ምክር ቤት ኢትዮጵያ ፣ ግብፅ እና ሱዳን በገጠሙት የግድቡ ዉዝግብ ላይ ለመነጋገር በሚያደርገው ስብሰባ ላይ #ኢትዮጵያን ይወክላሉ፡፡

በስብሰባው ላይም የኢትዮጵያን አቋም ያንጸባርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ኢትዮጵያን ከሚወክሉት ዶ/ር ኢ ር ስለሺ በቀለ በተጨማሪ በስብሰባዉ ላይ የግብፅና የሱዳን ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች የሚገኙ ይሆናል፡፡

ከሶስቱ ሀገራት ሚንስትሮች በተጨማሪ ፦
- በአፍሪቃ ቀንድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዩ መልዕክተኛ፣
- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአካባቢ ጥበቃ ኃላፊ
- የወቅቱ የአፍሪቃ ሕብረት ሊቀመንበር የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ዲፕሎማት ለተሰብሳቢዎች ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አል ዓይን አስነብቧል።

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ እና የጋና ፍልሚያ !

የሀገራችን የእግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ከደቂቃዎች በኃላ የጋና ብሄራዊ ቡድንን ይገጥማል።

ግጥሚያው ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ የሚደረግ #ማጣሪያ ሲሆን በጋና ኬፕ ኮስት በተባለው ስታዲየም ነው የሚደረገው።

በቋሚ አሰላለፍ ሀገራችን #ኢትዮጵያን የሚወክሉት ተጫዋቾች የታወቁ ሲሆን እነማን ናቸው የሚለውን በ https://publielectoral.lat/tikvahethsport/20410 መመልከት ይቻላል።

የሀገራችን ብሄራዊ የእግር ኳስ ቡድን አረጓንዴ ቁምጣ ፣ ቢጫ ካሶተኒ ቀይ የሚለብሱ ሲሆን ተፋላሚያችን ጋና ሙሉ ነጭ መለያ ይለብሳል።

ጨዋታውን ጥሩ የኢንተርኔት ግንኙነት ያላችሁ በFIFA ይፋዊ የዩቲዩብ ገፅ በዚህ 👉 https://t.co/j55uaSRXkI መመልከት ትችላላችሁ።

@tikvahethsport ደግሞ የጨዋታውን ሁኔታ እየተከታተለ በፅሁፍ ያሳውቃል።

መልካም ዕድል ለኢትዮጵያችን !

@tikvahethiopia
#USA

አምባሳደር ሳተርፊልድ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ።

አዲሱ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ #ኢትዮጵያን ጨምሮ ሱዳን እና ሳዑዲ አረቢያን እንደሚጎበኙ ተገልጿል።

አምባሳደር ሳተርፊልድ እኤአ ከጥር 17-20 ባሉት ቀናት ነው ሃገራቱን የሚጎበኙት፡፡

በቅድሚያ ወደ ሪያድ እንደሚጓዙ የሚጠበቁት ልዩ መልዕክተኛው ቀጥሎ ካርቱምንና አዲስ አበባን ይጎበኛሉ ተብሏል፡፡

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ረዳት ጸሃፊ ሞሊ ፊ አብረዋቸው ወደ ሃገራቱ እንደሚጓዙ ተገልጿል።

አምባሳደር ሳተርፊልድ በሪያድ ቆይታቸው በሱዳን ያለውን ወታደራዊ አገዛዝ እንዲያበቃ የሚጠይቁትን የለውጥ ኃይሎችን እንደሚያገኙና በመንግስታቱ ድርጅት አመቻችነት ለማካሄድ ስለታሰበው ሃገራዊ ውይይት እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል፡፡

ወደ ካርቱም ተጉዘው ከተለያዩ የለውጥና የዴሞክራሲ ኃይሎች ጋር እንዲሁም ከወጣት አደረጃጀቶች ጋር ይወያያሉ፡፡

በኢትዮጵያ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል።

መንግስት የተገኘውን የሰላም ጭላንጭል እንዲያጠናክር፣ የአየር ጥቃቶችን እንዲያቆም እና ሌሎችም መቃቃሮች እንዲያበቁ ማድረግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚነጋገሩም ነው የተገለጸው፡፡

ተኩስ እንዲቆም፣ እስረኞች አሁንም እንዲለቀቁና ሰብዓዊ እርዳታዎች ሳይስተጓጎሉ እንዲቀርቡ ይጠይቃሉ ተብሏል፡፡

መረጃውን #አል_ዓይን_ኒውስ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ዋቢ አድርጎ ነው በድረገፁ ላይ ያስነበበው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ም/ቤት ስብሰባ ተቀምጦ ነበር። በዚህም ም/ቤቱ በዩክሬን ጉዳይ የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ [የ193 አባል ሀገራት] አስቸኳይ ልዩ ስብሰባ እንዲጠራ በድምፅ ወስኗል። ስብሰባው ዛሬ ሰኞ ይካሄዳል። ሩስያ ስትቃወም [ድምፅን በድምፅ የመሻር /veto power/ መብቷ እዚህ ላይ ተግባራዊ አይሆንም] ፤ ቻይና ፣ ህንድ እና የተባበሩት አረብ…
#Update

የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ #ሩሲያን በማውገዝ እና ወታደሮቿን ከዩክሬን እንድታስወጣ በቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ዛሬ ድምፅ ሠጠ።

በዚህም ከ193 ሀገራት መካከል 141 ሀገራት ድጋፍ ሲሰጡ ፣ 5 ሀገራት ውሳኔ ሀሳቡን ተቃውመዋል፣ 35 ሀገራት ደግሞ ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል።

#ኢትዮጵያን 🇪🇹 ጨምሮ 13 ሀገራት በድምፅ አሰጣጡ ላይ ሙሉ በሙሉ አልተሳተፉም።

የውሳኔ ሀሳቡን የተቃወሙ ሀገራት ፦

🇷🇺 ሩስያ
🇧🇾 ቤላሩስ
🇪🇷 ኤርትራ
🇰🇵 ሰሜን ኮሪያ
🇸🇾 ሶሪያ ናቸው።

ድምፀ ተአቅቦ ካደረጉት መካከል ፦

🇩🇿 አልጄሪያ
🇦🇴 አንጎላ
🇧🇮 ቡሩንዲ
🇨🇬 ኮንጎ
🇨🇫 ማዕከላዊ ሪፐብሊክ አፍሪካ
🇲🇬 ማዳጋስካር
🇲🇱 ማሊ
🇳🇦 ናሚቢያ
🇲🇿 ሞዛምቢክ
🇸🇳 ሴኔጋል
🇸🇸 ደቡብ ሱዳን
🇸🇩 ሱዳን
🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
🇿🇼 ዝምባብዌ
🇺🇬 ዩጋንዳ
🇵🇰 ፓኪስታን
🇨🇺 ኩባ
🇮🇳 ህንድ
🇮🇷 ኢራን
🇮🇶 ኢራቅ
🇨🇳 ቻይና ይገኙበታል።

የውሳኔ ሀሳቡ በህጋዊ መንገድ አስገዳጅ ሳይሆን የተ.መ.ድ አባል ሀገራት እይታ የተንፀባረቀበት እና በሩስያ እና ቤላሩስ ላይ ጫና ለመፍጠር ያለመ ነው።

@tikvahethiopia
😢

ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ መሪዎች ተጎድተውም ቢሆን ኢትዮጵያን አንድ እንዲያደርጉ በእንባ ተማፀነች።

ኮማንደር ደራርቱ ተማፅኖዋን ያሰማችው በቤልግሬድ የአለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮን ላይ ከዓለም አንደኛ ሆኖ ላጠናቀቀው የአትሌቶች እና አሰልጣኞች ቡድን በተዘጋጀ የምስጋና ፕሮግራም ላይ ነው።

" የሀገራችን ጉዳይ ሁላችንንም ያመናል " ያለችው ደራርቱ " የትግራይ እናቶች አባቶች ፤ እናቶቻችን አባቶቻችን ናቸው በእርግጠኝነት ደግሞ ነገ ሌላ ቀን ነው ኢትዮጵያ ታርቃ አንድ ሆና ትቆማለች " ስትል ተናግራለች።

ኮማንደር ደራርቱ ፤ ከትግራይ ክልል የተገኙ ድንቅ አትሌቶችን ክብር ይገባችኃል ያለች ሲሆን " በብዙ ፈተናዎች አልፈው በብዙ ተፅእኖ አልፈው የኢትዮጵያን ባንዲራ ከፍ ስላደረጉ ምስጋና አቅርባለች።

" በእርግጠኝነት ቤተሰቦቻችሁ የት እንዳሉ ታውቃላችሁ " ያለችው ደራርቱ " ግድ የላችሁም እንወዳችኃለን እናከብራችኃለን ፤ እንደልጆቻችን ነው አሁንም የምናያችሁ ስለሆነም ትግራይ ዛሬ ብቻዋን አይደለችም ከኢትዮጵያ ጋር ነች፤ ነገም ከኢትዮጵያ ጋር ትሆናለች " ስትል ተናግራለች።

ኮማንደር ደራርቱ፤ የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ ክልላዊ መንግስት መሪዎች ተጎድታችሁም ቢሆን ለኢትዮጵያ ህዝብ ብላችሁ ኢትዮጵያን አንድ አድርጓት ስትል በእንባ የተማፀነች ሲሆን " ከእግዚአብሔር ጋር ትችላላችሁ። እናተ አንድ ካደረጋችሁ ኢትዮጵያ አንድ ትሆናለች። " ብላለች።

ኮማንደር አትሌት ደራርቱ አሜሪካ ፤ በ " H.R. 6600 " ኢትዮጵያንም ሆነ ትግራይን ለመጥቀም ሳይሆን ለመበተን እንደሆነ ተናግራ መሪዎች ከተስማሙ የሚፀድቅበት ምክንያት ስለሌለ ለወደፊት ኢትዮጵያ ሲሉ እዲስማሙ ተማፅናለች።

ህዝቡም በመተባበር #ኢትዮጵያን አንድ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርባለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መልዕክት_2 (ነገ የሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን ሂፍዝ ውድድር) - ፕሮግራሙ ከጠዋቱ 1 ሰዐት ጀምሮ ስለሚካሄድ በጊዜ አዲስ አበባ ስታዲየም እንገኝ። - በ500 ብር ትኬታ የቆረጠ ሁለት ሰው ሆኖ መግባት ይችላሉ። ትኬት ያልገዙ ሰዎች በ200 ብር በር ላይ እንዲገዙ ተመቻችቷል። - ሴቶች ከወጋገን ባንክ ፊት ለፊት ያሉትን በር ቁጥር 8፣ 9 እና 11ን ብቻ ተጠቀሙ። የVIP እንግዶችም በVIP…
ፎቶ ፦ በአሁን ሰዓት በ አዲስ አበባ ስታዲየም " ዓለም ዓቀፍ የቁርአን ሂፍዝ ውድድር " እየተካሄደ ይገኛል።

ፕሮግራሙ በርካታ ህዝበ ሙስሊም በተገኘበት ነው እየተከናወነ የሚገኘው።

በዚህ ዓለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ኢብራሒም አብዱራህማን ኢብራሒም ሀገራችን #ኢትዮጵያን 🇪🇹 ወክሎ የውድድሩ ተሳታፊ ነው።

ፕሮግራሙ እንደተጠናቀቀ ተጨማሪ መረጃዎችን የምንልክላችሁ ይሆናል።

@tikvahethiopia