TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ...

እኔ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነኝ!

#የዚችን_ሀገር_ችግር_የምቀርፈው_በመማር_ነው!

#መብቴን_የማስከብረው_በማወቅ_ነው

#ከምማርበት_ጊዜ_ቀንሼ_ለወንድሜ_ድንጋይ_አላነሳም!

#ይልቅስ_ጊዜ_ተርፎንም_ከሆነ_በጎ_ፈቃደኞች_ነን!

ትዝታዎቼን ከጥላቻ ጋር ማስተሳሰር አልሻም።ሰዎችን በመደገፍ ግን የተሻለ አለም ለወገኖቼ መፍጠር እሻለሁ! ጓደኞቼም እንደዛው!

ቀኖቻችንን ፍቅር በመስጠት ውስጥ እያሳለፍን ነው! ብዙ ፍቅራችንን የሚፈልጉ ወገኖች አሉ!

በመገፋፋት በታሪካችን ላይ የምናሰፍረው አንዳች መልካም አሻራ የለም!

እኛ ጋር ብትመጡ የምናወራችሁ እና የምናሳያችሁ መልካም ነገር እንጂ የተሰበረ መስታወት ፥የተጠቃ ተማሪ ፥ አይደለም እኛ በጎ ፍቃደኞች ነን!

#ጣሊታ_ራይዝ_አፕ #ሀምሊን_የፌስቱላ_ማዕከል
#ሀዋሳ_ዩኒቨርስቲ #አዋዳ_ካሞፓስ
#ቅን_ዲል_ክበብ

©ሀና ሀይሉ(አዋዳ TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ቅንነት ብዙ ጥቅም አለው፡፡ ፀሐይ በረዶን እንደሚያቀልጥ ሁሉ #ቅን መሆንም እንዲሁ አለመተማመን ፣ ጥላቻን እና አለመግባባትን ያተናል፡፡" ኢ/ር #ታከለ_ኡማ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ያስተዛዝባል...ቅን ልብ ቢኖረንስ??
(ውስጣችን ንፁህ ስላልሆነ ይሆን የምንፈራው?)

ይህን ፅሁፍ ያገኘሁት ከአንድ ከ200,000 በላይ ተከታዮች ካሉት የፌስቡክ ገፅ ነው። መልዕክቱ ብዙዎች ጋር ደርሶ ሰዎችን #መቀየር ይችላል ግን አይተን እንዳላየን ያለፍነው ብዙዎች ነን!! ሼር ያደረጉት እንኳን 13 ሰዎች ናቸው። ይሄኔ ግጭት፣ ረብሻ፣ የጦርነት ቅስቀሳ፣ የሀሰት ዜና...ቢሆን #በሺዎች የምንቆጠር ሰዎች ነበርን #ላይክ እና #ሼር የምናደርገው። ያሳዝናል! እውነት ሰላም እና ፍቅርን የምንፈልግ፤ እውነት #ፍትህ እና #እኩልነት የምንፈልግ ሰዎች ከሆንን ውስጣችን #ቅን ሊሆን ይገባዋል፤ ለሀገር እና ለህዝብ የሚጠቅሙ ነገሮችንም ማጋራት አለብን።

@tsegabwolde @tikvahethiopia