TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አምቦ #ለኩ #ጅማ #ከሚሴ #ይርጋለም #ሃዋሳ #ሶዶ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

#አዲስ_አበባ
0970514616/ዮናስ ገ/መስቀል/
0924140293/መባ/

#ሰበታ
0932540523/ያሬድ ለማ/
0921421493/ያብስራ ካሳ/

#መቐለ
0912178520/ኤርሚያስ ደጀኔ/
0923602445/ፊራኦል መስፍን/

#ራያ_ቆቦ
+251949256094/ሉላይ/

#ጅማ
0911670454/አሰፋ/

#ድሬዳዋ
0915034762/መሃሪ/

#አዳማ
0949377735/ሰላም/

#ሀዋሳ
+251926429534/ተስፋ/
+251935932153/ብስራት/

#ለኩ
0919687777/ዳዊት እንዳለ/

#ይርጋለም
0953804369-/አሸናፊ/
0964039768-ብርሀኑ/

#ከሚሴ
0915543171/ሁሴን/

#ወላይታሶዶ
+251913776084/Aso/
0926172318/Beza/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት ማህበራትና ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናሳውቃለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አዲስ_አበባ

በአዲስ አበባ ከተማ፣ የመድሃኒት ዕጥረት መባባሱን የሕክምና ባለሙያዎች ማኅበር ገልጿል፡፡ በተለይ የአስም፣ ስኳር እና ደም ብዛት መድሃኒቶች ዕጥረት አሳሳቢ መሆኑን የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ለሸገር ራድዮ ተናግረዋል፡፡ መድሃኒቶቹ ባንድ ወር ጊዜ ውስጥ #ያልቃሉ፡፡ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው መድሃኒት መጠንም በጣም #አነስተኛ ነው፡፡ ሐኪሞች የሚያዟቸው መድሃኒቶች በሕጋዊ መንገድ የገቡ ወይም ትክክለኛ መድሃኒት መሆን ይሁኑ አይሁኑም በቂ ማረጋገጫ የለም፡፡ መንግሥት ለመድሃኒት ግዥ በቂ የውጭ ምንዛሬ እንዲመድብም ማኅበሩ ጠይቋል፡፡

Via ሸገር 102.1/wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አዲስ_አበባ_ከተማ_አስተዳደር

ባለዲግሪው መፃህፍት አዟሪ በብልሽት ለረጅም ጊዜ ቆሞ የነበረ ተሽከርካሪ ለስራ እንዲሆነው ከከተማ አስተዳደሩ ተበረከተለት!

ከተመረቀ በኋላ ለአራት አመታት መፃህፍት በማዞር ህይወቱን ሲመራ የነበረው ወጣት አንዷለም ይስሃቅ ከከተማ አስተዳደሩ ለረጅም ጊዜ ቆሞ የነበረ ተሽከርካሪ በኢ/ር ታከለ ኡማ ተበርክቶለታል።

ወጣቱ ደርሶበት በነበረው የአእምሮ ህመም ችግር ሳይበገር እና ስራ ጠባቂ ሳይሆን እራሱን ለመለወጥ ያደረገው ጥረት ለብዙዎች አርአያ የሚሆን እንደሆነም ተነግሯል።

በጥቂት ጊዚያት ውስጥም በከተማዋ ያለ አገልግሎት የቆሙ ሌሎች 700 የሚሆኑ አንበሳ የከተማ አውቶብሶችን ወደ ተንቀሳቃሽ ሱቆች በመቀየር በከተማዋ ለሚገኙ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ለመስጠት ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።

ይህ ተግባር በአንድ በኩል የከተማ አስተዳደሩ ለወጣቶች ስራ የመፍጠር ግዙፍ እቅድ አካል ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በችግሮች ሳይበገሩ ራሳቸውን ለመቀየር እየሞከሩ ያሉ ወጣቶችን ለማበረታታት አላማ ያደረገ ተግባር ነው።

Via #mayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እሁድን በበጎ ተግባር!

#አዲስ_አበባ

💫የአንድ እሽግ ለአንድ ልጅ የሙዚቃ ድግስ ነገ እሁድ ነሃሴ 26 በጌትፋም ሆቴል ይደረጋል። መግቢያ: 12 ደብተር - 2 እስክርቢቶ - 2 እርሳስ - 2 መቅረጫ እና 2 ላጲስ - የTIKVAH-ETH የአ/አ ቤተሰቦች እንዳትቀሩ! #onepackforonechild

💫Rotaract Ethiopia በጎ ስራ ላይ የተሰማራ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ሲሆን ለአዲሱ አመት #አልባሳት እያሰባሰበ ነው እናተም ተሳተፉ ያላችሁበት መጥተው ይወስዳሉ ደውሉላቸው Rotaract club of Atrons President Yeabsera --- +251922175164. (Or Natnael -@Natysf +251923594536, Sofonias - @SophoDarik +251 92 453 9140

#ወላይታ_ሶዶ

💫"አለን ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ" ላለፉት ሁለት ቀናት ለ800 ተማሪዎች ለትምህርት የሚሆናቸውን ቁሳቁስ እያሰባሰበ ነው። በተጨማሪ የደም ልገሳ እየተደረገ ይገኛል። ነገም ለ3ኛ ቀን ይቀጥላል። ወላይታ ሶዶ ያላችሁ የTIKVAH-ETH ተከታዮችም እሁዳችሁን ከነሱ ጋር ማሳለፍ ትችላላችሁ። ስልክ +251913776084፣ 0926172318

#ሻሸመኔ

💫የሻሸመኔ ወጣቶች ነገ የይደግ በጎ አድራጎት ማእከልን ይጎበኛሉ እንዲሁም ግቢውን ያፀዳሉ። የሻሸመኔ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች ኑ እሁድን በመልካም ስራ እናሳልፍ ከሰአት 8:00 ሰአት ላይ CDI እንገናኝ ብለዋችኃል!! ስልክ፦0926940304

#ለኩ
💫በለኩ ከተማ የሚገኙ "እኔም ለወገን" የበጎ አድራጎት ማህበር አባላት የሻይ ቡና ፕሮግራም አዘጋጅተዋል። የለኩ ቤተሰቦቻችን እሁድን አብራችሁ!0986241726

💫"ነገ በለኩ ፉርቃን የአበባ እና የችግኝ መተከል ስነ ስርአት ስለሚኖረን የቻላችሁ ከጥዋቱ 3 ሰአት በለኩ ፉርቃን ግቢ በመገኘት አሻራችሁን እንድታሳርፉ ጀመአችን ጥሪውን ያስተላልፋል" ቢላል የለኩ ሙስሊም በጎ አድራጎት ጀመአ

#ድሬዳዋ

💫"የድሬዳዋ ስካውት ካውንስል አባላት ነን በከተማችን የሚገኙ መንገዶች በግራና በቀኝ ያሉ ጠርዞችን ነጭ እና ጥቁር ቀለም በመቀባት ለመንገዱ ውበት እንዲሁም በምሽት ለአሽከርካሪዎች በቀላሉ እንዲታይ በማድረግ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስ አንፃር የበኩላችንን እየተወጣን ነው ። ስራው ገና አልተጠናቀቀም ነገም እለተ ሰንበት ይቀጥላል።"

#ወሊሶ

💫ወገኔን ለማስተማር እሮጣለሁ በከተማችን ቅን ወጣቶች የተቋቋመው የ" we are one" የበጎ አድራጎት ማህበር ባሳለፍነው አመት "ወገኔን ለማስተማር እኔም እሮጣለሁ" በሚል መሪ ቃል ታላቅ የእሩጫ ዉድድር ማሰናዳቱ የሚታወስ ነዉ። በዘንድሮ አመትም በተመሳሳይ መሪ ቃል በአይነቱ ልዩ በሆነ ሩጫ ዝግጅቱን አጠናቆ እርሶን እየጠበቀ ይገኛል ታድያ እርሶም የሩጫ ቲሸርት በመግዛት ከአላማችን ጎን ይሰለፉ። የቲሸርቱ ዋጋ 100 ብር የቲሸርቱ መገኛ ቦታ: ፓስታ ቤት፣የኛ ህንፃ ፣ክርኪስ እናም ሁሉም ቦታ አዙረው በመሸጥ ላይ ከሚገኙ አባላቶች

በሌሎች አካባቢዎች ያሉ እንቅስቃሴዎችን እንደደረሰኝ አቀርባለሁ!
#አዲስ_አበባ

በሞሮኮ አስናጋጅነት በተካሄደው 12ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በ13 የስፖርት አይነቶች የተሳተፈው የኢትዮጵያ የስፖርት ልኡካን ትናንት ሌሊት አዲስ አበባ የገባ ሲሆን በአዲስ አበባ ስታዲየም ይፋዊ አቀባበል እየተደረገለት ይገኛል፡፡

በአቀባበል ስነ-ስርአቱ ላይ የኢትዮጵያ ስፖር ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር አቶ ጌታቸው ባልቻ፣ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ እና ከኢትዮጵያ አትሌቲከስ ፌዴሬሽን የተውጣጡ አካላት ተሳታፊ ናቸው፡፡

የስፖርት ልኡካን ቡድኑ አዲስ አበባ የገባበት ሰአት ለአቀባበል ምቹ ስላልነበረ የአቀባበል ስነ-ስርዓቱ ለዛሬ መተላለፉ ተገልጿል፡፡ 250 አባላትን የያዘው የስፖርት ልኡካን ቡድኑ በሞሮው መድረክ 6 የወርቅ፣ 5 የብር እና 12 የነሃስ ሜዳሊያዎች በማስመዝብ ከአፍሪካ 9ኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

Via ኢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አዲስ_አበባ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ለመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ለመስጠት ቃል የገባችውን 1 ሚሊየን ደብተር ዛሬ አስረከበች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የቤተ ክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በተገኘበት ዛሬ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ 1 ሚሊየን ደብተር አስረክበዋል። በዚህም ወቅት ብፁእነታቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ “ለተማሪዎቻችን መልካም አዲስ ዓመት እና መልካም የትምህርት ዘመንን እንመኛለን” ብለዋል። ኢንጂነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው “ቤተ ክርስቲያኗ ስንሳሳት ስታርመን፤ ጥሩ ስንሰራም ስታበረታታን መጥታለች ለዚህም እናመሰግናለን” ብለዋል። አሁን ላይ ቤተክርስቲያኗ ባጋጠማት ነገር ሳትሸነፍ አቃፊ እንደመሆኗ በዚሁ ይህንን ጊዜ እንደምታልፍ እምነታቸው መሆኑን እና የከተማ አስተዳደሩም ከጎኗ መሆኑን ነው የተናገሩት።

Via #FBC

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አዲስ_አበባ

በአዲስ አበባ የነበረው የኢሬቻ በአል አከባበር ባማረ መልኩና በሰላም ተጠናቋል። ይህን አስመልክቶም የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ለከተማዋ ነዋሪዎችና ለበአሉ አከባበር አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ የምስጋና መልእክት አስተላልፈዋል።

ኢንጂነር ታከለ በሁሉም የከተማዋ ጫፎች የሚገኙ የከተማዋ ነዋሪዎች ያሳዩት ትብብር የሚደነቅና የሚከበር ነው ብለዋል። በአሉን ለማክበር ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡትን በልዩ ፍቅርና ያላቸውን በማቅረብም ጭምር አክብሮታቸውን ስላሳዩም ለከተማዋ ነዋሪዎች ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።

የከተማዋ ባለሀብቶችም የበአሉን አከባበር በመደገፍ በአሉ እውን እንዲሆን ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋናን አቅርበዋል። በበአሉ ላይ አንድም የጸጥታ ችግር እንዳይፈጠር በበቂ ዝግጅትና በሀላፊነት ስሜት በብቃት ለሰሩ የጸጥታ አካላትም ምስጋናን አቅርበዋል።

ለጸጥታው መከበር ወጣቶች ያሳዩትንም ተሳትፎና ትብብርም የሚደነቅ ነው ብለዋል ኢ/ር ታከለ ኡማ። ኢንጂነር ታከለ ኡማ በአጠቃላይም አዲስ አበባ ህብረብሄራዊነቷን በጠበቀና ባማረ መልኩ የኢሬቻ በአል በመዲናዋ እንዲከበር ድጋፍ ላደረጉና በጨዋነት ለተባበሩ በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋናቸውን መግለፃቸውን የከንቲባ ፅሀፈት ቤት አስታውቋል።

Via Mayor Office AA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥንቃቄ!

#አዲስ_አበባ

ፓስፖርት እስከ 3 ወር እንደሚያቆይ ይታወቃል። ነገር ግን የተለያዩ አጭበርባሪዎች ፓስፖርት ለማውጣት የሚመጡ ሰዎችን ፓስፖርት 3 ወር ስለሚቆይ አፋጣኝ ፓስፖርት አለ ነገር ግን ለዚህ አገልግሎት 6,000 ብር መክፈል አለባችሁ በሚል እያጭበረበሩ እንደሚገኙ ይዚህ ሰለባ የሆኑ የቲክቫህ ቤተሰቦች ተናግረዋል። ይህን የሚፈፅሙ ሰዎች ኢሚግሬሽን ውስጥ የሚሰራ ሰው እንዳላቸው በማስመሰል ስልክ ይደውላሉ፤ ገንዘብም በውጭ ሆነው ይቀበላሉ።

አንድ ወንድማችን የጋጠመው፦

"እኛ መኪና ጋር ተላላኪ ነኝ ብሎ የመጣ አንድ ልጅ እዛው ካፌ ውስጥ እንደሚሰራ ይነግረናል [ይህ ገንዘብ ተቀባዩ ነው]። ውስጥ ያለው ልጅ [ኢሚግሬሽን ነው የምስራው ነው የሚለው] ደግሞ ብሩን ለሱ ስጡትና እኔ ጋር ኑ፤ እኔ አሚግሬሽን በር ላይ እጠብቃችኃለሁ ይለናል። ልጁ ፖስታ ይሰጣችኃል። ፖስታውን ሳትከፍቱት ይዛችሁ ኑ ይለናል።

ምንድነው ዋስትናችን ብለን ስንጠይቀው ምንም ችግር የለውም አትጠራጠሩ ብሎ የተለያዩ ምክንያቶችን ይደረድራል። ከዛም እኛ ብሩን አንሰጥም ሁለት ስለሆንን ጓደኛዬ አንተ ጋር ትምጣ እኔ ደግሞ እዚህ ሆኜ ብሩን ለልጁ ልስጠው አለኩት። [ልጁን ስታገኘው ብሩን ለልጁ ለመስጠት ነበር] ይህ ግን አይቻልም አይሆንም አለ።

በመጨረሻ ብር እንደማንሰጣቸው ሲያውቁ በቃ ብሩን አትስጡት ኑ እኔ ጋር በር ላይ ጠብቃችኃለሁ ይለናል ኢሚግሬሽን ውስጥ ነው የምስራው ያለን ሰውዬ ከዛም ስንሄድ ምንም ሰው አላገኘንም።

ስልካችንን ብሎክ አደረጉት። እዛው አካባቢ ሰልፍ ከያዙ ሰዎች ስንጠይቅ አንድ ሰው እኔንም ከዚህ በፊት አንዲት ሴት ልጅ 6000 ብር በልታኛለች ብሎ ነገረን። ሌሎች ጥንያቄ ያድርጉ። ህጋዊ መንገድ ብቻ ተከትለው ፓስፖርት ለማውጣት መሄድ አለባቸው።"

@tikvahethiopia
* 2 የችሎት ጉዳዮች !

#አዲስ_አበባ

የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠ/ኤታማዦር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንንና ሜጀር ጄነራል ገዛኢ አበራን በመግደል በፍ/ቤት ጥፋተኛ የተባለው አስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ በሞት እንዲቀጣ ጠይቋል።

የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዛሬ አርብ ጥያቄውን ያቀረበው የአስር አለቃ መሳፍንትን የክስ ሂደት ለሚመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው። 

ዐቃቤ ህግ ዛሬ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ባለ 3 ገጽ የቅጣት አስተያየት፤ በተከሳሹ ላይ ሶስት የቅጣት ማክበጃዎችን ጠቅሷል።

የተከሳሽ ጠበቆች ፥ ተከሳሽ ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የለበትም ብለዋል። ዐቃቤ ህግ “አንድም [የወንጀል] ሪከርድ ሳያቀርብ የሞት ፍርድ መጠየቁ ከህጉ ያፈነገጠ ነው” ሲሉ የአቃቤ ህግን የቅጣት አስተያየት ተቃውመዋል። 

ፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለሰኔ 21 /2013 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በዝርዝር ያንብቡ : telegra.ph/Ethiopia-Insider-06-18

#ባህርዳር

ዛሬ አርብ ማለዳ የባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት የዋለው ችሎት በሰኔ 15ቱ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ግድያ እጃቸው አለበት የተባሉ 55 ተከሳሾች ላይ ብይን ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ በሻምበል መማር ጌትነት የክስ መዝገብ ስማቸው የተዘረዘሩ 55 ተከሳሾች ውስጥ 6ቱ በሌሉበት፣ 49 በተገኙበት ፍርዳቸው ሲታይ የነበረ ሲሆን ዛሬ ፍርድ ቤቱ 20ዎቹን በነጸ አሰናብቷል።

በነጻ እንዲሰናበቱ ከተበየነላቸው ተከሳሾች መካከል አቶ ዘመነ ካሴ ይገኙበታል።

በዝርዝር ያንብቡ : telegra.ph/BBC-06-18-2

መረጃዎቹ ከኢትዮጵያ ኢንሳይደር እና ከቢቢሲ የተውጣቱ ናቸው።

@tikvahethiopi
#አዲስ_አበባ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ላለፉት ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን ፖሊሳዊ የደንብ ልብስ እና ዓርማ መቀየሩን ምክንያት በማድረግ የማብሰሪያ መርሀ-ግብር ማዘጋጀቱን ዛሬ አስታውቋል።

ይህ መርሀግብር ነገ ቅዳሜ ሰኔ 12/2013 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ ነው ይካሄዳል የተባለው።

በዚህ ምክንያት ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6 ሰዓት ድረስ የተወሰኑ መንገዶች ለትራፊክ ዝግ ይሆናሉ ተብሏል።

በዚህም መሰረት ፦

• ከኡራኤል ወደ መስቀል አደባባይ
• ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ
• ከ4ኛ ክፍለ ጦር/ጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
• ከሀራምቤ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ
• ከለገሃር ወደ መስቀል አደባባይ
• ከብሄራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ እና በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ መጋቢ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች ይህን አውቀው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ተብሏል።

መረጃውን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ነው ያገኘነው።

@tikvahethiopia