TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሰበር_ዜና #ባህር_ዳር

በአማራ ክልል የተሞከረው መፈንቅለ መንግስት #መክሸፉን አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተናግረዋል። ይህንን ድርጊት በፈፀሙት ላይ #እርምጃ እንዲወሰድ ትእዛዝ ተሰጥቷል፤ እንቅስቃሴም ተጀምሯል ሲሉ ገልፀዋል።

Via #etv/#Elias_Meseret/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የመፈንቅለ መንግስት ሙከራው የአማራን ህዝብና ክልል የማይመጥን አሳፋሪና አሳዛኝ ክስተት ነው" :- አቶ ደመቀ መኮንን
----------------------------------------------------------------------
ዛሬ በአማራ ክልላዊ መንግስት የተቃጣው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እና ጥቃት የአማራን ህዝብና ታሪክ የማይመጥን አሳፋሪና አሳዛኝ ክስተት እንደሆነ የኢፌዲሪ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ። አቶ ደመቀ ከአሜሪካ በሰጡት መግለጫ ጉዳዩን የፌደራልና የክልል አካላት በቅርበት እየተከታተለው ሲሆን ተጠያቂ አካላት ለህግ እንዲቀርቡ ይደረጋል ብለዋል። ህብረተሰቡም ውዥንብር ውስጥ ሳይገባ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ አቶ ደመቀ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

Via #etv
Pic #elias_meseret
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#RIDE

"ይህንን ደንብ አንቀበለውም፣ ከፍርድ ቤት እገዳ ለማስወጣት ሂደት ላይ ነን" የራይድ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ሳምራዊት

/ልዩ መረጃ-- ከኤልያስ ጋር/

የራይድ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ሳምራዊትን የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮ ይፋ ስላደረገው አዲሱ መመሪያ፦

"ሲጀመር የትራንስፖርት ቢሮው ይህን መመሪያ ማውጣት ይችላል ወይ የሚለው ላይ ጥያቄ አለ፣ ምክንያቱም እኛ የቴክኖሎጂ ድርጅት ስለሆንን የሚመለከተው የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ነው። በእኛ እምነት የትራንስፖርት ቢሮው ይህ ስልጣን የለውም። ሲቀጥል በRide ስር ከ 6,000 በላይ አባላት አሉ፣ የሚጎዱት እነዚህ ሰዎች ጭምር ናቸው። ይህ መመሪያ ሲወጣ እኛን ማሳተፍ ነበረበት። ሌላው ቀርቶ ረቂቁን እንኳን አላየነውም። በአጠቃላይ ይህንን ደንብ አንቀበለውም፣ ከፍርድ ቤት እገዳ ለማስወጣት ሂደት ላይ ነን። በሌለ infrastructure አንድን ድርጅት እዚህ ማድረስ ቀላል አልነበረም። ይህንን ሁሉ ስራ ሰርተን እዚህ ስንደርስ appreciate መደረግ ነበረብን። በትራንስፖርት ቢሮ የተደረገው ግን እኛን የሚቃረን ነው። እንደዚህ አይደረግም! ይህ ፈፅሞ መቆም ያለበት ነገር ነው። ይብቃ! ወጣቱ ይስራ! ሀገሪቱንም ያሳድግ! በዚህ አጋጣሚ ኢንጅነር ታከለ እና አቶ እንዳወቅ እየደገፉን ነው ያሉት። (የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮው) ዶ/ር ሰለሞን ግን ትንሽ ቆም ብለው አስበው ከእኛ ጋር ቢሰሩ ጥሩ ነው። ብዙ ልምድ አለን። ምን አልባት ልምድ የላቸውም ብለው አስበው ከሆነ ተሳስተዋል።"

Via #ELIAS_MESERET
@tsegabwolde @tikvahethiopia