TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሳዛኝ_ዜና⬇️

በሶማሊያ የፑንትላንድ የንግድ ከተማ በሆነችው ቦሳሶ ውስጥ ሦስት #ኢትዮጵያዊያን #በአይሲስ ታጣቂዎች #ሲገደሉ ቢያንስ አንድ መቁሰሉ ተዘገበ።

ስለጥቃቱ በቀዳሚነት የወጡ ዘገባዎች እንዳመለከቱት ታጣቂዎቹ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ይኖሩበታል በሚባለው ሳንቶስ ተብሎ በሚጣራው የከተማዋ ክፍል ውስጥ ባገኟቸው አራት ኢትዮጵያዊያን ላይ #ተኩስ ከፍተው ነው ጥቃቱን የፈፀሙት።

አንድ ስማቸውን ያልጠቀሱ የአካባቢው ባለስልጣን ኢትዮጵያዊያኑ በተፈፀመባቸው ጥቃት መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ለቢቢሲ ሲያረጋግጡ፤ አፍቃሬ አይኤስ የሆነ ቡድንም በትዊተር ገጹ ላይ ስለጥቃቱ አስፍሯል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ ሃገራት የኤደን ባህረ ሰላጤን በትናንሽ ጀልባዎች በማቋረጥ ወደ የመንና የመካከለኛው ምሥራቅ ሃገራት በህገ ወጥ መንገድ ለመሻገር የሚፈልጉ ስደተኞች #የቦሳሶን የባህር በር ይጠቀማሉ።

በአካባቢውም በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንደሚገኙ ተገልጿል።

እነዚህ በጥቃቱ የሞቱትና የቆሰሉት ኢትዮጵያዊያንም በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች አማካይነት ባህሩን ተሻግረው በጦርነት ወደ የምትታመሰው #የመን ለመጓዝ በቦታው የነበሩ ስደተኞች እንደሆኑ ይታመናል።

አይሲስ ከቅርብ ወራት ወዲህ በጉልህ የሚታዩ በርካታ ጥቃቶችን በሶማሊያ ውስጥ እየፈፀመ ሲሆን በተለይ ደግሞ በፑንት ላንድ ግዛት ውስጥ የአይኤስ ቡደን ከሌሎች አካባቢዎች በበለጠ ሰፊ እንቅስቃሴ ያደርጋል ተብሎ ይታመናል።

ፑንትላንድ በሰሜን ሶማሊያ የምትገኝ ከፊል ራስ ገዝ የሆነች ግዛት ናት።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በሞያሌ ከተማ ዛሬም #ተኩስ እንደሚሰማ DW ተፈናቃይ ዜጎችን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ተፈናቃዮች ከሞያሌ ሸሽተው ወደ ሜጋ ከተማ ሸሽተዋል፡፡ ተፈናቃዮቹ ከሕዝብ ከሚየገኙት ድጋፍ በስተቀር ቀይ መስቀልም ሆነ መንግሥት እስካሁን ምንም ዐይነት አስቸኳይ ዕርዳታ
አላደረሱላቸውም፡፡

©wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንደ ውሃ እና ሸዲ ከተሞች፣ የመንግስት ወታደሮች መንገድ በዘጉ ወጣቶች ላይ በከፈቱት #ተኩስ 5 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን 3 ሰዎች ክፉኛ ተጎድተው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል። ከሟቾቹ መካከል የ10 አመት ታዳጊ ይገኝበታል። ግጭቱ የተፈጠረው አካባቢውን ለቆ በመውጣት ላይ የሚገኘውን የሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ማሽነሪዎችን ለማጀብ የመጡ ወታደሮች ተኩስ ከፍተው ሰዎችን ከገደሉ በኅላ ነው።

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ላይቭ ሀፕዴት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ታጣቂዎች ሁለት ሰዎችን ገደሉ‼️

በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ዛሬ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ሁለት ሰዎች መገደላቸውን የዐይን ዕማኝ እና የወረዳው ባለሥልጣን አስታወቁ። ጥቃቱ የተፈጸመው ወረዳውን ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን በሚያዋስነውና #ጎልቤ በተባለ ሥፍራ ላይ ነው።

ጥቃቱን ተከትሎ በአካባቢው የሚገኘው መከላከያ ሠራዊት ወደ ሥፍራው በመንቀሳቀስ #ከበባ ማድረጉ ታውቋዋል፡፡ በሥፍራው የነበሩ የአይን እማኝ እንዳረጋገጡት ሠራዊቱ በሥፍራው ከመድረሱ አስቀድሞ የታጠቁ ቡድኖች ወደ መንደሩ በመግባት በነዋሪዎች ላይ #ተኩስ ከፍተዋል፡፡

አንድ የመንደሩ ነዋሪ "አማሮ ወረዳ ጎልቤ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ልዩ ስሙ ላፊፋ በተባለ ቦታ ነው ታላቅ ወንድሜ እና የታላቅ ወንድሜ ልጅ ከብት ከሚጠብቁበት ከማሳቸው ገብተው ጨፈጨፏቸው በቀብር ሥርዓት ላይ ነን ያለንው" ሲሉ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ ተናግረዋል።

የአማሮ ልዩ ወረዳ አስተዳደር የባህል ፤ ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ #አማረ_አክሊሉ "ዛሬ አራት ሰዓት ገደማ ላይ ነው የጸረ-ሰላም ኃይሎች ሰዎች የገደሉት። ታጣቂዎቹ ወደ አማሮ ወረዳ ጎልቤ ቀበሌ የመጡት ከገላና ወረዳ በኩል ነው" ሲሉ ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠዋል። ኃላፊው በሰራዊቱ ክትትል ውስጥ መሆናቸውን የተረዱት ታጣቂዎቹ በገላና ሸለቆ ውስጥ ገብተው #መሰወራቸውንና ሠራዊቱም ወደ ጦር ሰፈሩ መመለሱን ገልጸዋል፡፡ "መከላከያ ሰራዊቱ ሁለት ሰው ከሞተ በኋላ መጥቶ ነበር። መከላከያ ሰራዊቶች መጥተው ክትትል አድርገው አላገኟቸውም። ወደ ኋላ ተመልሰው ወደ ካምፓቸው ተመልሰዋል። ታጣቂዎቹን ሊያገኟቸው አልቻሉም። ጫካ ነው የገቡት" ሲሉ አቶ አማረ ሁኔታውን ለጀርመን ራድዮ ጣቢያ አስረድተዋል።

በአካባቢው በተፈጸመው ጥቃትና በተካሄደው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ እስከአሁን ከአገር መከላከያ ሚኔስቴርም ሆነ ከፌደራሉ መንግሥት የተሰጠ #ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም፡፡

በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ካለፈው የሰኔ ወር ጀምሮ የታጠቁ ሀይሎች በተደጋጋሚ በሚፈጽሙት ጥቃት እስከ አሁን ሰማኒያ አራት ሰዎች ሲሞቱ በመቶዎች የሚቆጠሩ ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን ከወረዳው አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ምንጭ:- የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከባህር ዳር...

"ፀግሽ ባህርዳር የርዕሰ መስተዳድሩ ቢሮ አካባባቢ ከፍተኛ #ተኩስ እየተሰማ ነው። መንገዱም ተዘግቷል። Becky ከባህርዳር"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠቅላይ ኤታማዞር ሹሙ ጀኔራል ሰዓረ መኮንን ከተገደሉ በኋላ ተጨማሪ ሃይል ወደ ቦታው ሲያመራ ከሁለት የታጠቁ ሰዎች #ተኩስ እንደተከፈተበት ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ዜና ምንጩ መረጃውን ያሰፈረው ወደ ጀኔራሉ ቤት ሁኔታውን ለመቆጣጠር ከሄዱት ጸጥታ ሃይሎች መካከል አንደኛውን ባልደረባ ጠቅሶ ነው፡፡ የጀኔራሉ አጃቢ ጀኔራሉን #እንደገደለ አንደኛው ባካባቢው ቆሞ በሚጠብቀው መኪና ተሳፍሮ አምልጧል፤ ሌላኛው በተተኮሰበት ጥይት ከቆሰለ በኋላ በራሱ አንገት ላይ ተኩሶ ራሱን ለማጥፋት ቢሞክርም በጸጥታ ሃይሎች ቁጥጥር ስር ውሏል-ብሏል ዘገባው አክሎ፡፡

Via #wazema
🗞ሰኔ 20/10/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሁንም የተኩስ ድምፅ ይሰማል!

#በጎንደር ከተማ ዙሪያ ዛሬም #ተኩስ እንደሚሰማ አሥራት ቲቪ ዘግቧል፡፡ ከከተማው ዳርቻ፣ ቁስቋም ደብር አካባቢ አሁንም ተኩስ እንደሚሰማ ነዋሪዎች ለጣቢያ ተናግረዋል፡፡ ተኩስ ልውውጡ ለቅማንት ሕዝብ መብት እንታገላለን የሚሉ ከጭልጋ አቅጣጫ በመጡ ታጣቂዎች እና በክልሉ ልዩ ሃይል መካከል እንደሆነ ዘገባዎች ያመለክታሉ፡፡

Via ዋዜማ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
የእስራኤልና ፍልስጤሙ ሃማስ ጦርነት በቀጣይ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን ?

ዋና ነጥቦች ፦

▪️ሃማስ ፤ " ወራሪ " ናት በሚላት #እስራኤል ላይ  ወታደራዊ ኦፕሬሽን ማካሄድ መጀመሩንይህ ኦፕሬሽንም #ፍልስጤማውያን ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለደረሰባቸው ግፍ ሁሉ ምላሽ እንደሆነ ገልጿል።

▪️ እስራኤል ፤ " አሸባሪ " የምትለው የሃማስ ቡድን ጥቃት መክፈቱ ከባድ ስህተት መሆኑን በመግለፅ ለእያንዳንዱ ድርጊቱ የከፋ ዋጋ እንደሚከፍልበት ፤ ለሚመጣው ነገር  ሁሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስድ ገልጻለች። ሃማስ ላይም መጠነ ሰፊ የአፀፋ እርምጃ ጀምራለች።

▪️እስካሁን ከእስራኤል ከ700 በላይ ከፍልስጤም ከ400 በላይ ሰዎች አልቀዋል።

በእስራኤል እና ሃማስ ጦርነት ሀገራት እና መሪዎች አቋማቸውን እያንፀባረቁ ናቸው።

አንዳንዶቹ በግልፅ ሃማስን " የሽብር ቡድን " እንደሆነ ገልፀው ጥቃቱን ሲያወግዙ አንዳንዶቹ ደግሞ በሁለቱም በኩል ግጭት ቆመ በእርጋታ ነገሮች እንዲፈቱ እየጠየቁ ነው።

እስራኤል አጋሮቿ ሁሉ የተከፈተባትን ጥቃት በግልፅ እንዲያወግዙ ትሻለች።

በወታደራዊና ኢኮኖሚ አቅማቸው ጠንካራ የሆነ የዓለም ሀገራት ምን አቋም ነው የያዙት ?

🇺🇸አሜሪካ - የእስራኤል ወዳጇ #አሜሪካ የ ' ሃማስን ' ጥቃት የአሸባሪዎች ጥቃት ነው በማለት በግልፅ ጥቃቱን አውግዛ ለእስራኤል ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አደርጋለሁ ብላለች። ወታደራዊ ድጋፍም ልካለች።

🇫🇷ፈረንሳይ - የሃማስን ጥቃት " የአሸባሪዎች ጥቃት " ስትል ገልጻ ከእስራኤል ጎን እንዳሆነች ገልጻለች።

🇩🇪ጀርመን -ጥቃቱን አውግዛ ከእስራኤል ጎን መሆኗን ገልጻለች። ሃማስንም አሸባሪ ስትል ጠርታለች።

🇮🇳ሕንድ-እስራኤል የተፈፀመባት ጥቃት የአሸባሪዎች ጥቃት ነው ብላ ከእስራኤል ጎን መሆኗን ገልጻለች።

🇬🇧ዩናይትድ ኪንግደም - በእስራኤል ላይ " የሽብር " ጥቃት መፈፀሙን ገልጻ ሀገሪቱ እራሷን የመከላከል መብት አላት ብላለች። ከእስራኤል ጎን እንደሆነችም ገልጻለች።

_

🇮🇷ኢራን - " የፍልስጤም ህዝብ #ራሱን_የመከላከል መብት አለው " ብላ የሃማስን ጥቃት በግልፅ " አኩሪ ተግባር " ስትል አወድሳለች።  " ፍልስጤም እና እየሩሳሌም " ነፃ እስኪወጡ ከፍልሥጤም ተዋጊዎች ጎን እንቆማለን ብላለች።
_

🇨🇳ቻይና- ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት እንዲረጋጉ ፤ ራሳቸውን እንዲቆጣጠሩ እና ጦርነቱን በአስቸኳይ እንዲያቆሙ እንዲሁም ሲቪሎች እንዲጠበቁ ፤ የሁኔታውን እንዳይባባስም እንዲሰሩ አሳስባለች።

ቤጂንግ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ የቻይና አቋምን በተመለከተ እስራኤል ሃማስ ላደረሰው ጥቃት ከቻይና ጠንካራ ውግዘት ጠብቃ ነበር ብሏል።

ቻይና የሃማስ ታጣቂ ኃይልን እንደ አሸባሪ ድርጅት ሳይሆን እንደተቃዋሚ ኃይል ነው የምታየው።

🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ - ሀገሪቱ በቅርቡ ከእስራኤል ጋር ያላትን ግንኙነት ለማደስ እየተንቀሳቀሰች ሲሆን አሁን የተቀሰቀሰው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቅርባለች። ሁለቱም ወገኖች ግጭት እንዲያቆሙና ሲቪሎችም እንዲጠበቁ አሳስባለች።

🇦🇪የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) - ያለው ሁኔታ እጅግ እንዳሳሰባት በመግለፅ ግጭት እንዲቆም እና ሲቪሎች እንዲጠበቁ ስትል ጥሪ አቅርባለች።

🇹🇷ቱርክ - በእስራኤልና ፍልስጤም ሃይሎች መካከል የሚካሄደውን ጦርነት ለማረጋጋት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንደምታደርግ አቋሟን ገልጻለች። ለሁለቱ ሀገራት መፍትሄ ቀጣናዊ ሰላም ማስፈን ብቸኛ መንገድ ነው ብላለች። አሁን ላይ ያለው ከፍተኛ ውጥረት እንዲረግብ እንደምትሰራ ነው የገለፀችው።

🇷🇺 ሩስያ - ሩስያ በአቸኳይ #ተኩስ_እንዲቆም ጥሪ አቅርባለች።

_

አፍሪካውያን ምን አሉ ?

- የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የሆኑት ሙሣ ፋኪ ማሃማት " የእሥራዔል-ፍልስጥዔም ቋሚ ውጥረት ዋናው ምክንያት የፍልስጥዔም ህዝብ መሠረታዊ መብቶቹን፣ በተለይም ነፃና ሉዓላዊ መንግሥት መነፈጉ ነው " ብለዋል። ሁለቱ ኃይሎች ግጭት አቁመው ወደ ድርድር ጠረጴዛ ይቅርቡ ብለዋል።


- የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቨኒ " በእሥራዔል እና በፍልስጤም መካከል እንዳዲስ ግጭት መቀስቀሱ የሚያሳዝን ነገር ነው። ለምን ሁለቱም ወገኖች የሁለት መንግስት መፍትሄን ተግባራዊ አያደርጉም? በተለይ ደግሞ ሰላማዊ ዜጎችን እና ተዋጊ ያልሆኑ አካላት በታጣቂዎች ዒላማ መደረጋቸው መወገዝ አለበት " ብለዋል።

- #ኬንያ በፕሬዜዳንቷ በኩል ባወጣችው መግለጫ እስራኤል ላይ የተፈፀመው የሽብር ጥቃት መሆኑን በመግለፅ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች ገልጻለች።   በተጨማሪ ግጭቱ እንዲበርድ እና እስራኤልም ፍልስጤምም ከወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ብላለች።

የUN ፀጥታ ም/ቤት ስብሰባ በምን ተጠናቀቀ ?

ትላንትና ምሽት የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በእስራኤል - ጋዛ ጦርነት በዝግ አስቸኳይ ስብሰባ ቢቀመጥም አባል ሀገራቱ መስማማት ስላልቻሉ የጋራ መግለጫቸውን ማውጣት አልቻሉም።

አሜሪካ 15ቱ የፀጥታው ምክር ቤት አባላት #ሃማስን አጥብቀው እንዲያወግዙ መጠየቋ ተሰምቷል።

የአሜሪካው ከፍተኛ ዲፕሎማት የሆኑት ሮበርት ዉድ ፤ " የሃማስን ጥቃት ያወገዙ ብዙ አገሮች አሉ። ሁሉም እንዳልሆኑ ግልፅ ነው " ያሉ ሲሆን " እኔ ምንም ሳልናገር ከመካከላቸው አንዱን ማወቅ ትችላላችሁ " ሲሉ ሩስያ ጥቃቱን ካላወገዙት ውስጥ እንደሆነች ተናግረዋል።

መረጃዎቹ ከዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የተሰባሰቡ ናቸው።

@tikvahethiopia