TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሐምሌ_22

ኢትዮጵያ ቡና

ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ ሰኞ በሙሉ ኢትዮጵያ ከተማዎች እንደሚተከል ይጠበቃል። ሁላችንም የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ማልያ በመልበስ ከጠዋቱ 1:00–1:30 በተመደበልን ቦታ በሰአቱ በመገኘት ቀጥታ የክለባችንን አሻራ ለሀገራችን እናሳርፍ።

የመሳፈርያ ቦታዎች፦

#ፒያሳ_መዘጋጃ
#ሜክሲኮ_ቡና_እና_ሻይ
#መስቀል_አደባባይ
#ጀሞ
#ሳሪስ_አደይ_አበባ
#ሰባተኛ_ቶታል

#ኢትዮጵያ_ቡና @BUNA_GEBEYA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ 📣

➡️ #ካሜሮን፦ በካሜሩን መገንጠልን አላማቸው አድርገው ይንቀሳቀሳሉ የተባሉ ታጣቂዎች ናይጄሪያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ መንደር በፈጸሙት ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል። ጥቃቱ ባሳለፍነው እሁድ በደ/ምዕራብ የካሜሩን ክፍል ኦቦኒ ሁለት በተሰኘ መንደር የተፈፀመ ሲሆን ከሞቱ ሰዎች ባሻገር ከ60 በላይ ሰዎች ቆስለዋል። ታጣቂዎቹ ነዋሪዎቹ በየወሩ ገንዘብ እንዲከፍሏቸው ይፈልጋሉ፤ ነዋሪዎቹ ደግሞ ፍቃደኛ አልሆኑም። ለዚህም ነው ጥቃት ያደረሱባቸው ተብሏል።

➡️ #ሜክሲኮ ፦ በደቡባዊ ሜክሲኮ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ በትንሹ 10 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የገቡበትን ማወቅ እንዳልተቻለ ተሰምቷል።

➡️ #ቻይና ፦ የሻንጋይ ነዋሪዎች ከሁለት ወር በኃላ የኮቪድ-19 የእንቅስቃሴ ገደብ መነሳቱን ተከትሎ ነፃ ሆነዋል። ነዋሪዎች ባለፉት 2 ወር ኮቪድ-19ኝን ለመከላከል በተጣለ የእንቅስቃሴ ገደብ ምክንያት ከእንቅስቃሴ ርቀው ቆይተዋል።

➡️ #ዩክሬን ፦ የየክሬን ኬርሰን ግዛት በሩስያ ቁጥጥር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ሁሉንም የግንኙነት መስመሮች እንዲዘጉ ማድረጋቸው ተነግሯል።

➡️ #አሜሪካ ፦ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ሀገራቸው ለዩክሬን 'ቁልፍ ኢላማዎችን' ለመምታት የሚያስችላትን እጅግ የዘመኑ ሮኬቶችን እንደምትልክ አሳውቀዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ ወደ ባይዶዋ እንደሚሄዱ የተነገረላቸው አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፕሬዝዳንት ከሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት መሪ አብዲአዚዝ ሀሰን ሞሀመድ እና ከባህላዊ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ፕሬዜዳንቱ ወደ ባይዶዋ ያደረጉት ጉዞ ዳግም ፕሬዜዳንት ሆነው ከተመረጡ በኃላ የመጀመሪያቸው ነው።

#ቲአርቲ #ቢቢሲ #ፍራንስ24 #ሲጂቲኤን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#BGI #PurposeBlack

" ነገ ጥዋት መግለጫ እንሰጣለን "- ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያን አ/ማ

በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ ተቋርጧል።

ቢጂአይ-ኢትዮጵያ በባከልን ኢሜል የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅ እና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎትና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ነው።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ምን አስተያየት አለው የሚለውንና የሚሰጠው ምላሽ ይኖር እንደሆነ ለድርጅቱ ኃላፊዎች ስልክ ደውለንላቸው የነበረ ሲሆን ዝርዝር መረጃ ባይሰጡም ነገ ጥዋት 2 ሰዓት ይፋዊ መግለጫ / ምላሽ እንደሚሰጡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ድርጅቱ የሚሰጠውን መግለጫ ተከታትለን መረጃ እንልካለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BGI #PurposeBlack " ነገ ጥዋት መግለጫ እንሰጣለን "- ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያን አ/ማ በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ ተቋርጧል። ቢጂአይ-ኢትዮጵያ በባከልን ኢሜል የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል…
#PurposeBlack

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ምን አለ ?

- የቢጂአይ ኢትዮጵያ የዋናው መሥሪያ ቤት ሽያጭ ውልን በውልና ማስረጃ በኩል ለመፈጸም ዝግጁ ነን።

- ቢጂአይ ኢትዮጵያ የመንግስትን ግዴታ ቀድሞ ባለመወጣቱ በውል እና ማስረጃ መፈራረም አልተቻለም። ከታክስ ጋር በተያያዘ ክሊራንስ አልጨረሱም።

- ቢጂአይ ብዙ ማሟላት ያለበትን ዶክመንት አላሟላም። በዚህ ምክንያት በውል እና ማስረጃ ለመፈራረም አልፈለጉም።

- ለቢጂአይ 1 ቢሊዮን 150 ሚሊዮን ብር ክፍያ ፈፅመናል። ቀሪውን ገንዘብ በውልና ማስረጃ ስንፈራረም ለመክፈል ዝግጁ ነን።

- ክፍያው በ3 ዙር የሚፈፀም ሲሆን 2ኛው ዙር ክፍያ የሚፈጸመው በውልና ማስረጃ ስንፈራረም ነው። ይህ ቀድሞ በፈጸመው ውል ላይ ተቀምጧል።

- ከታክስ ነፃ የሆኑበት ወረቀት ከቀረበ በውልና ማስረጃ እንፈራረማለን። እኛ ተገቢውን ዶክመት ካሟሉ በሁለተኛ ዙር የሚጠበቅብንን 2.5 ቢልየን ብር ለመክፈል ዝግጁ ነን።

- ቅዳሜ የካቲት 23 /2016 ዓ.ም በውልና ማስረጃ እንዋዋል የሚል ደብዳቤ ልከንላቸው ነበር። እነሱ ሕጋዊ  መስፈርቶችን ማሟላት ባለመቻላቸው ውሉን አቋርጠናል የሚል መግለጫ ትናንት አውጥተዋል።

- እኛ ብሩን ለመክፈል ዝግጁ ነን በውልና ማስረጃ የማይፈራረሙ ከሆነ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንወስዳለን።

- ኃላፊነቱን እየተወጣ ያልሆነው በውልና ማስረጃ እንዲፈፀም ኃላፊነቱን ያልተወጣው ቢጂአይ ኢትዮጵያ እንጂ እኛ አይደለንም።

- አሁንም ግዢውን ለመፈፀም ዝግጁ ነን።

- ሌላ አማራጭ መሬቶችን ገዝተናል። መሰረት እየጣልን ነው። በገባነው ቃል ቤቶቹን በሚቀጥሉት 5 አመታት ሰርተን እናስረክባለን።

- ከመንግስት በሊዝ ስምምነት እንዲሁም 30/70 በሚል ስምምነት በግዢ ሂደት ላይ ያሉ መሬቶችም አሉ።

- ቤት ለመሸጥ ቃል ለገባንላቸው ደንበኞች ቤቱን እናስረክባለን።

በትላንትናው ዕለት ቢጂአይ-ኢትዮጵያ በላከልን ኢሜል አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ መቋረጡን ማሳወቁ ይታወሳል።

የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅ እና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎትና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ እንደሆነ መግለፁ አይዘነጋም።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#PurposeBlack የፐርፐርዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አፈፃሚ ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ በአሁን ሰዓት #አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ተነግሯል። " አሜሪካ የሚገኙት ለስራ ነው " ያለው ድርጅቱ የፊታችን ሀሙስ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱና መግለጫም እንደሚሰጡ አመልክቷል። ዛሬ መግለጫ ሰጥተው የነበረው የድርጅቱ የቦርድ አባል እና የህግ አማካሪ ዶ/ር ኤርሚያስ ብርሃኑ ናቸው። ፐርፐዝ ብላክ ከቤቶቹ ግንባታ…
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ መግለጫ ሰጠ።

በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡን ተከትሎ ከሁለቱም ወገን መግለጫዎች መውጣታቸው ይታወሳል።

ቢጂአይ ኢትዮጵያ ውሉ ስለመቋረጡ ከገለጸ በኋላ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሰጠው መግለጫ ላይ በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ህግ ክፍሉ ዳይሬክተር አቶ ነጋ ምህረቴ እንዲሁም የህግ አማካሪ የሆነው "ምህረታብ እና ጌቱ አድቮኬትስ ኤል ኤል ፒ" መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው ላይ የተነሱ ጉዳዮች ምንድናቸው ?

- የድርድር ሂደቱ 8 ወራት ፈጅቷል። ቀድመን የተፈራረምነው የቀብድ ውል ነው። የቀብድ ውሉ የጊዜ ገደቡ ሦስት ወር ቢሆንም በእኛ በኩል በቅንነት 8 ወራት ጠብቀናል።

- ቀብድ ውሉን ከተፈራረምን በኋላ በእኛ በድርጅታችን ኃላፊ ጭምር እንዲሁም የመክፈል አቅም እንዳላቸው በተደጋጋሚ ማስረጃ እንዲሰጡን ብንጠይቅም እንከፍላለን ከሚል ደብዳቤ በስተቀር የሚጠበቅባቸውን ብር ለመክፈል አቅም እንዳላቸው ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም።

- ግብር ለመክፈል ወደኋላ የምንል አይደለንም። የሚሸጠውም ህንጻ እዳ ያለበት አይደለም ቢጂአይ እዳ ያለበት ንብረት ለሽያጭ አያቀርብም።

- ካፒታል ጌን ኪሊራንስ ለማውጣት በቅድሚያ የሽያጭ ውል መሟላት አለበት። ይህ በሌለበት ሁኔታ ክሊራንስ ማውጣት አንችልም። ይህ በህጉ የተቀመጠ የታወቀ አሰራር ነው። ቢጂአይ ክሊራንስ ለማምጣት ዝግጁ ቢሆንም ነን በቀብድ ውሉ በተጠቀሰው መሰረት በቅደም ተከተል በተቀመጠው መሰረት የሽያጭ ውሉ ላይ መስማማት ያስፈልጋል። የተለያዩ ውይይቶች ቢደረግም እሱን መፈረም አልቻሉም።

- በቀብድ ውሉ መሰረት የተከፈለው 1 ቢሊዮን ብር +15 VAT ሲሆን ቀጣዩን ክፍያ ለመክፈል የሽያጭ ውሉን መፈረም እንዲሁም በውልና ማስረጃ ሌሎች የሚያስፈልጉ ዶክመንቶች ቀርቦ እንዲጸድቅ ይጠበቃል። ይህንን ለማድረግ ከሚያስፈልገው አንዱ የሽያጭ ውል ሲሆን ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ይህንን መፈረም ባለመቻሉ ውሉን ለማቋረጥ ተገደናል።

- ከፐርፐዝ ብላክ ጋር ያለን ውል ተቋርጧል። ዳግም ተመልሰን የምንደራደርበት ነገር የለም። ይህ ውል ከተጠናቀቀ በኋላ ህንጻውን የመሸጥ አሁንም ፍላጎት አለን።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia