TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#BGI #PurposeBlack

" ነገ ጥዋት መግለጫ እንሰጣለን "- ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያን አ/ማ

በቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ መካከል ሲካሄድ የቆየው አ/አ #ሜክሲኮ የሚገኘው የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ድርድር ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ ተቋርጧል።

ቢጂአይ-ኢትዮጵያ በባከልን ኢሜል የሽያጩ ውል የተቋረጠው ፤ በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅ እና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎትና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ነው።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ምን አስተያየት አለው የሚለውንና የሚሰጠው ምላሽ ይኖር እንደሆነ ለድርጅቱ ኃላፊዎች ስልክ ደውለንላቸው የነበረ ሲሆን ዝርዝር መረጃ ባይሰጡም ነገ ጥዋት 2 ሰዓት ይፋዊ መግለጫ / ምላሽ እንደሚሰጡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ድርጅቱ የሚሰጠውን መግለጫ ተከታትለን መረጃ እንልካለን።

@tikvahethiopia