TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሰበር_ዜና የቀድሞው የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም የነበሩት ጄኔራል ኣብርሃም ወልደማርያም /ኳርተር/ በታይላንድ በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

ጄኔራል ኣብርሃ ኢትዮጵያ ከነበሯት 4 ባለ ሙሉ ጄኔራሎች አንዱ የነበሩ ሲሆን የሌላውን ጄኔራል ሰዐረ መኮንን ህልፈት ተከትሎ የሙሉ ጄኔራሎች ቁጥር በአንድ ሳምንት ወደ ሁለት ዝቅ ብሏል። በስራ ላይ ያሉ ሙሉ ባለ ሙሉ ጄኔራል ደግሞ አንድ ብቻ ሆነዋል።

ለሟች ነፍስ ይማር ለቤተሰብ መፅናናት ይሁን!
Via #Petros_Ashenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቢልለኔ ስዩም የፌስቡክ ገፅ የላትም!

#Billene_Seyoum ይህ የfacebook page #ሀሰተኛ ነው። ይህንን ጉዳይ የAPው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ከዚህ ቀደም ከራሳቸው አንደበት አረጋግጧል። ዋልታና የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ጨምሮ በርካቶች የቢልለኔ ስዩምን ፌስቡክ በመጥቀስ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የፊታችን ማክሰኞ የዩኔስኮን ፌሊ ሁፉዌ ብዋኚን የሰላም ሽልማት እንደሚቀበሉ እየገለፁ ነው።

ለመረጃ ያህል...

የፊታችን ማክሰኞ ጁላይ 9 የሽልማት ስነስርዓት #አይካሄድም። ጠቅላይ ሚንስትሩም ወደ ፈረንሳይ ፓሪ አይጓዙም። እርግጥ ነው ሜይ 2 ቀን 2019 ዩኔስኮ ጠቅላይ ሚንስትሩ የሰላም ሽልማቱን ማሸነፋቸውንና ጁላይ 9 ቀን ሽልማቱን እንደሚቀበሉ ገልፆ የነበረ ቢሆንም፤ አሁን ግን ለጊዜው የሽልማቱን መስጫ ቀን "ላልተወሰነ" ጊዜ ማራዘሙን ለማረጋገጥ ተችሏል። /#Petros_Ashenafi/

@tsegabwolde @tikvahethiopia