TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አዲስ አበባ⬆️በአሸዋ ሜዳና በተለያዩ አካባቢዎች የጠፈጠረው ግድያና ዝርፊያን #በመቃወም መንግስት ፍትህ ይስጠን በማለት በአዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች ሰላማዊ ሰልፍ እየተደረገ ነው። ፌደራል ፖሊስና መከላከያ በአንዳንድ ቦታ ላይ #እርምጃ እየወሰዱ ነው።

©ይህ ዘገባ የአሀዱ FM ነው!
@tsegabwolde
አሳይታ⬆️በአፋር ክልል የአሳኢታ ከተማ ወጣቶች የክልሉን መንግስት #በመቃወም በትላንትናው ዕለት ሰልፍ አድርገዋል።

ፎቶ እና ቪድዮ፦ TIKVAH-ETHIOPIA(መሀ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰመራ⬆️በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ፣ የክልሉን መንግስት #በመቃወም አደባባይ በወጡ ነዋሪዎች ላይ የክልሉ ልዩ ሀይል በወሰደው እርምጃ ቢያንስ አምስት ሰዎች እንደተጎዱ ተሰምቷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ገንደውሃ🔝

ትናንት መከላከያ ሰራዊት በምዕራብ ጎንደር ዞን የፈጸመውን ግድያ #በመቃወም በመተማ ገንደውሃ የተቃውሞ ሰልፍ በመደረግ ላይ ይገኛል። ሰልፈኞቹ ሰራዊቱ አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ጠይቀዋል። ሰልፈኞቹ መከላከያ 'ሪፎርም' ሊደረግ የማይችል ተቋም ስለሆነ፣ የሰራዊቱ አባል የሆኑ የአማራ ብሔር ተወላጆች ከሰራዊቱ እራሳቸውን እንዲያገሉም ጠይቀዋል።

Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አማራ ክልል‼️

በአማራ ክልል የትራፊክ ደህንነት መቆጣጠሪያ ህግን #በመቃወም የትራንስፖርት አገልግሎት #ተስተጓጉሏል፡፡

የክልሉ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ውቤ አጥናፉ ለኢዜአ እንደገለጹት የትራንስፖርት አገልግሎቱ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ተስተጓጉሏል።

በተለይም ከባህር ዳር አዊ፣ ምዕራብ ጎጃም፣ ምስራቅ ጎጃምና በእነዚህ መስመሮች ያሉ የትራንስፖርት አገልግሎት በመቋረጡ ህዝቡ መጉላላት እየደረሰበት መሆኑን ተናግረዋል።

ለአገልግሎቱ መቋረጥም ከጥር 1/2011 ዓ.ም. ጀምሮ ይተገበራል የተባለውን የ "ኤስ ኤም ኤስ" የትራፊክ ደህንነት መጠበቂያ ህግ በመቃወም እንደሆነ አመልክተዋል።

ሆኖም የቅድመ ዝግጅትና የስልጠና ስራዎች #ባለመጠናቀቃቸው ህጉን ተግባራዊ ማድረግ #እንዳልተጀመረ ጠቁመው፥ "ይህን #ሰበብ አድርጎ አገልግሎት ማቋረጥ ተቀባይነት የለውም" ብለዋል።

በህጉ ዙሪያ ለአስፈፃሚ ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠት መጀመሩን አመልክተው በቀጣይ ለአሽከርካሪዎች፣ ለባለሃብቶችና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠርና የማሳወቅ ስራ በማከናወን እንደሚተገበር አስታውቀዋል።

ህግ የሚወጣው የአብዛኛውን የህብረተሰብ ክፍል ደህንነት ለመጠበቅ እንጂ የተወሰኑ ሰዎችን ፍላጎት ለማሟላት እንዳልሆነ ተናግረው ህጉ አሁን በሰው ህይወት እየደረሰ ያለውን አደጋ ለመቀነስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

አሁን ችግሩን ለመፍታትና አገልግሎቱን ለማስጀመር ከአሽከርካሪ ማህበራትና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ ነው ብለዋል።

የዓባይ መደበኛ ደረጃ አንድ የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ዓባይነህ ማህሪ በበኩላቸው ለትራንስፖርት አገልግሎቱ መቋረጥ ማህበሩ እውቅና እንደሌለው ገልጸዋል።

የ"ኤስ ኤም ኤስ" ህግን በሚመለከት ቀደም ሲል ውይይት ማድረጋቸውን አስታውሰው፤ ሆኖም ይተገባራል የሚል መረጃ እንደሌላቸውና ሙሉ እውቅና ያልተፈጠረበት መሆኑን ጠቅሰዋል።

አሽከርካሪዎቹ አገልግሎት እንደማይሰጡ ያሳወቀ አካል እንደሌለ የገለጹት ደግሞ የዘንባባ ደረጃ ሁለት የህዝብ ማመላለሻ ባለንብረቶች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ በላይ አፈወርቅ ናቸው።

"ገና ይተገባራል የሚባለውን የኤስ ኤም ኤስ የቅጣት ሪከርድ ህግ ቀድሞ በመፍራት የስራ ማቆማ ተገቢ አይደለም ፤በዚህ የተነሳም ህዝብ መጉላላት የለበትም" ብለዋል።

በአማራ ክልል 61 የአሽከርካሪ ማህበራት ያሉ ሲሆን ሰባት ሺህ 300 አገልግሎት የሚሰጡ መለስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ተሽከርካሪዎች እንዳሉም ታውቋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር🔝

ትናንት መከላከያ ሰራዊት በምዕራብ ጎንደር ዞን የፈጸመውን ግድያ #በመቃወም በባህርዳር ከተማ ሰልፍ ተደርጓል። እንዲሁም ከቤኒሻንጉል ጉምዝ እና ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው በባህርዳር የተጠለሉ ዜጎች መንግስት ይረዳቸው ዘንደ ለመጠየቅ ሰልፍ ተደርጓል።

via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መንገዶች ተከፍተዋል‼️

በአፋር የነበረው የመንገድ መዝጋት #አድማ #እንደተጠናቀቀና መንገዶች #እንደተከፈቱ ተገልጿል፡፡ ሶማሊ ነዋሪዎች የሚበዛባቸው ሶስት ቀበሌዎች ላይ እየተፈጠረ ያለውን #ግጭት ለማርገብ በሚል ከቀበሌዎቹ የአፋር ክልል ልዩ ሃይል #እንዲወጣ መደረጉን #በመቃወም ነበር የክልሉ ወጣቶች ተቃውሞ የጀመሩት፡፡ የተቃውሞ እንቅስቃሴው ተጓዦችንም ሆነ ንብረቶቻቸው ላይ ምንም አይነት #ጉዳት_ያላደረሰ ነበር፡፡ከአዋሽ ወደትግራይ የሚወስደው መንገድ ትላንት ጠዋት 2 ሰዓት ላይ የተከፈተ ሲሆን ከመሃል አገር ወደምስራቅ ኢትዮጵያና ወደ ጂቡቲ የሚወስዱት መንገዶችም ተከፍተዋል፡፡

Via VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትግራይ ክልል ምክር ቤት‼️

የትግራይ ክልል ምክር ቤት በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀውን የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ #በመቃወም ውሳኔ አስተላለፈ።

ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው በመቐለ ከተማ እያካሄደ ባለው 5ኛ ዓመት 14 መደበኛ ጉባዔው ነው።

ምክር ቤቱ በውሳኔ ሀሳቡ አዋጁ የፌዴራል መንግስት በክልሎች ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የክልላዊ አስተዳደር መብትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣንን እንዲጋፋ የሚያደርግ ነው ብሏል።

በተጨማሪም በክልሎች፣ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች መካከል #መጠራጠር እንዲፈጠር የሚያደርግ እንደሆነም ነው ምክር ቤቱ በውሳኔ ሀሳቡ የገለፀው።

ለዚህም ኮሚሽኑ የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች በሕገ መንግስት የተሰጣቸውን ስልጣን ተክቶ የወሰንና የማንነት ጉዳዮችን ለመመልከት መቋቋሙ ስሕተት ነው ሲል በውሳኔ ሀሳቡ አስፍሯል። ምክር ቤቱ በመጨረሻም አዋጁን በመቃወም የተዘጋጀውን የውሳኔ ሀሳብ አፅድቋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተቃውሞ ሰልፉ ሳይካሄድ ቀረ‼️

በቅርቡ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የጸደቀውን የስደተኞች አዋጅ #በመቃወም በጋምቤላ ክልል ተወላጆች ዛሬ በአዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሎ የነበረው ሰልፍ ፍቃድ ባለማግኘቱ ሳይካሄድ ቀርቷል። ረፋድ 3፡30 ገደማ ከ35 እስከ 40 የሚሆኑ የጋምቤላ ክልል ተወላጆች በመስቀል አደባባይ ቢሰባሰቡም ፍቃድ ያገኙበትን ደብዳቤ ለጸጥታ አስከባሪ ፖሊሶች ማቅረብ ባለመቻላቸው ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል። የጸደቀው አዋጅ በጋምቤላ ክልል ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩ እና፣ ህዝቡ ተወያይቶ #መግባባት ላይ ያልደረሰበት መሆኑ ሰልፍ ለማድረግ እንዲነሳሱ እንዳደረጋቸው በቦታው የጀርመን ድምፅ ራድዮብያነጋገራቸው ወጣቶች ተናግረዋል። በተመሳሳይ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ሊካሄድ የነበረው ሰልፍም የከተማ አስተዳደሩ አሁን ያለው የክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ሰልፍ ለማድረግ የሚያስችል ባለመሆኑ ፈቃድ አልሰጥም በማለቱ አለመከናወኑን የጀርመን ድምፅ ራድዮ በስልክ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪ #አረጋግጠዋል

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፍኖተሰላም🔝

በአማራ ክልል #ምዕራብ_ጎጃም_ዞን #የፍኖተሰላም ከተማ ነዋሪዎች የመሬት ወረራን #በመቃወም ድምፃቸውን አሰምተዋል።

#ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክሱም ዩኒቨርሲቲ...
.
.
.
አለመረጋጋቱ የተከሰተው ባለፈው ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ምክንያቱ እስካሁን ባልታወቀ ድርጊት የአንድ ተማሪ ሕይወት ማለፉን ተከትሎ የተወሰኑ ተማሪዎች በአክሱም ዩኒቨርሲቲ አመጽ ለማስነሳት በመሞከራቸው ነው ተብሏል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የተማሪዎቹ ድርጊት ተገቢነት እንደሌለው ሲመክር ቢሰነብትም ግጭት ተፈጥሮ የአንድ ተማሪ ሕይወት አልፏል፡፡

ግጭት እንደቀሰቀሱ ታምኖ እርምጃ የተወሰደባቸው ተማሪዎች እንዳሉና እርምጃው ተገቢ አለመሆኑን #በመቃወም ሌሎች ተማሪዎች ማታ ማታ ይረብሹ እንደነበርና ከትናንት ግንቦት 27 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ቀን ላይ ግጭት መቀስቀሱን በስፍራው የሚገኙ የዓይን እማኞች ለአብመድ አረጋግጠዋል፡፡

በዚህም የአንድ ተማሪ ሕይወት አልፏል፡፡ ተማሪዎቹ ግን ሁኔታው #ስላልተረጋጋ ስንት ተማሪዎች እንደተጎዱ መረጃ እንደሌላቸው ነው የተናገሩት፡፡

አሁን ላይ ሁኔታውን ለማረጋጋት የመከላከያ ሠራዊት አባላት ወደ ዩኒቨርሲቲው መግባታቸውንም ነው የዓይን እማኞች የተናገሩት፡፡
.
.
የትግራይ ክልል የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዩች ቢሮ የአንድ ተማሪ ሕይዎት ማለፉን #ከመስማት ውጪ ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃ እንደሌለው ነው ያሳወቀው፡፡ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ሁኔታውን ለማረጋጋት ከተማሪዎች ጋር ዛሬ ጥዋት ተወያይቷል።

ምንጭ፦ አብመድ
ፎቶ፦ TIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዛሬም ሰልፍ እየተደረገ ይገኛል!

የመከላከያ ሰራዊት የሰጠው ምላሽ ተገቢ አይደለም ያሉ፤ እንዲሁም በንፁሃን ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት #በመቃወም የአፋር ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች በተለያዩ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች እየተደረጉ ይገኛሉ።

Via Abu Jaefar Dalol
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የግብፁ መሪ የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግብፅን እንዲጎበኙ ግብዣ አደረጉ። ከቀናት በፊት ለሶማሊያው ፕሬዜዳንት ተመሳሳይ መልዕክት መላካቸው ይታወሳል። የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሽኩሪ በኤርትራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በአስመራ ቆይታቸው ከፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተገናኝተው ነበር። በዚህም ወቅት ከፕሬዜዳንት አልሲሲ የተላከ መልዕክት አድርሰዋል…
የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ዛሬ ግብፅ ካይሮ ገብተዋል።

ካይሮ ሲደርሱ የግብፁ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ሁለቱ አካላት በሁለትዮሽ እና በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሏል።

ከወራት በፊት የግብፁ መሪ የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ግብፅን እንዲጎበኙ ግብዣ ማድረጋቸው ይታወሳል።

ግብፅ ግብዣውን አቅርባ የነበረው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ሳሜህ ሽኩሪ በኤርትራ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ነው።

ሚኒስትሩ ወደ ኤርትራ ለጉብኝት የሄዱት የኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመና ከማንም ቀድማ ስምምነቱን #በመቃወም አቋሟን ካሳወቀች በኃላ ነው።

ለኤርትራው መሪ ግብዣ ከመቅረቡ ቀደም ብሎ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት በኤርትራ ጉብኝት እያደረጉ በነበረበት ወቅት የግብፁ ፕሬዜዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ተመሳሳይ ግብፅን ይጎብኙ የሚል መልዕክት ማድረሳቸው አይዘነጋም።

@tikvahethiopia