TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አዲስ_አበባ: "መልካም ወጣት ለኢትዮጵያ #አንድነት 2011" የተሰኘ በአገልጋይ #ዮናታን_አክሊሉ የሚዘጋጅ የወጣቶች መርሃ ግብር #በትላንትናው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በተገኙበት መከፈቱ ተሰምቷል። በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና የገቢዎች ሚንስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተገኝተው ነበር።

🗞ቀን ሃምሌ 4/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ ያመለጠው የኮቪድ-19 ታማሚ!

የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ በኮቪድ-19 መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ሰባት (7) መሆናቸውን ገልጿል።

ከነዚህ ሰባት (7) ሰዎች መካከል አንደኛው ከአዲስ አበባ ከተማ #አምልጦ የተያዘ እንደሆነ ቢሮው በዛሬው ዕለታዊ መግለጫው ጠቁሟል።

ይህ ከአዲስ አበባ ከተማ አምልጦ የተያዘው ግለሠብ #በትላንትናው ዕለት የጤና ሚኒስቴር አዲስ በቫይረሱ መያዛቸው ካረጋገጠው 61 ሰዎች ውስጥ አንደኛው ነው።

ግለሠቡ በጉራጌ ዞን ማረቆ ወረዳ ላይ ተይዞ እዛው በይቶ ማቆያ እንዲቆይ ተደርጓል። ከግለሰቡ ጋር ንክኪ የነበራቸው 30 ያህል ሰዎች ተለይተው በማቆያ ውስጥ እንደሚገኙ የክልሉ ጤና ቢሮ አሳውቋል።

በነገራችን ላይ በደ/ብ/ብ/ህ/ክ መንግስት ባለፉት 24 ሰዓት 76 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በቫይረሱ የተያዘ ሰው #አልተገኘም። እስካሁን በአጠቃላይ ለ1,072 ሰዎች ምርመራ ተደርጓል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia