TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሁለት ሳምንት በኋላ ወደ ሶማሊያ #ሞቃዲሾ በረራ ይጀምራል። አየር መንገዱ በሳምንት ሶስት ጊዜ ሰኞ ረቡዕ
እና ዓርብ ወደ ሞቃዲሾ ለመብረር እቅድ ይዟል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️

በሶማሊያ ዋና ከተማ #ሞቃዲሾ በተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የፈንጂ ጥቃት፣ የሰው ሕይወት አለፈ፡፡ በዛሬው ዕለት ከሶማሊያ ፖሊስ ኃይል የወንጀል ምርመራ ክፍል አቅራቢያ በሚገኘው የሳሃፊ ሆቴል እና በአካባቢው በደቂቃዎች ልዩነት የፈነዱት #ቦምቦች አራቱን አንጋቾች ጨምሮ ሃያ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን የዓይን ዕማኞችና የሕክምና ባለሥልጣናት አመልክተዋል።

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE የኢትዮጵያ የኤርትራና የሶማሊያ መሪዎች ቀጣይ የሶስትዮሽ ውይይታቸውን #ሞቃዲሾ ላይ ለማካሄድ መስማማታቸው ታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በረራው ተቋርጧል‼️

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ40 ዓመት በኃላ ወደ ሶማሊያ #ሞቃዲሾ ጀምሮት የነበረውን በረራ #ማቋረጡን ሸገር FM ዘገበ።

ተጨማሪ፦ ከትናንት በስትያ ዜግነቱ እንግሊዛዊ የሆነ ግለሰብ ከሞቃዲሾ ወደ አዲስ አበባ የሚመጣ በረራ ላይ #ተቀጣጣይ ነገር ይዞ ሊገባ ሲሞክር በኤርፖርት ጥበቃዎች #ተይዟል#ከአልሽባብ የሽብር ቡድን ጋር ግንኙነት ሊኖረው ይችላል ተብሎም ተገምቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም ከደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ #ላልተወሰነ ጊዜ በረራውን አቋርጧል ሲል ሸገር ምንጮቼ ነገሩኝ ብሎ ዘግቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update መቅዲሹ፤ በደረሰው ጥቃት 19 ተገደለዋል። ትናንት ምሽት በአጥፍቶ ጠፊ የቦምብ ፍንዳታ በደረሰባት የሶማሊያ ዋና ከተማ #ሞቃዲሾ ዛሬም ተኩስ መቀጠሉ እየተነገረ ነው። በፍንዳታው የደረሰውን ጨምሮ እስካሁን ቢያንስ 29 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል። በርካቶችም ተጎድተዋል። ትናንት ምሽት አንድ አጥፍቶ ጠፊ እንቅስቃሴ በሚበዛበት መንገድ ዳር ከሚገኝ ሆቴል አቅራቢያ በመኪና ውስጥ ባጠመደው ፈንጂ ራሱን ሲያጋይ እሳቱ ተዛምቶ ጉዳቱን እንዳሰፋውም ተጠቅሷል። ከፍንዳታው በኋላ የሶማሊያ ኃይሎች በአካባቢው ወደ አንድ ሕንፃ ተጠግተው ከመሸጉ #የአልሸባብ ታጣቂዎች ጋር መታኮስ መቀጠላቸውንም ተገልጿል። ሆቴሉ ውስጥ የአልሸባብ ታጣቂዎች ሰላማዊ ሰዎችን አግተው መቆየታቸውን የሶማሊያ መንግሥት የዜና አውታር ዘግቧል። የሀገሪቱ የፀጥታ ኃይል ባልደረባ አብድራህማን አሊ ለፈረንሳይ የዜና ወኪል የተጎዱ ሰዎችን የማዳን ሥራ እየተከናወነ መሆኑን፣ ተኩሱ በመቀጠሉም የሟቾች ቁጥርም ሊጨምር እንደሚችል አመልክተዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዛሬ #ሞቃዲሾ ውስጥ ከሶማልያው ፕሬዚዳንት ቤተ መንግሥት አቅራቢያ ከሚገኝ ምግብ ቤት ውጭ ዛሬ የደረሰ የመኪና ቦምብ ፍንዳታ በትንሹ ለ5 ሰዎች ሕይወት መጥፋትና ሌሎች ዘጠኝ መቁሰል ምክንያት መሆኑ ተገለፀ። የጥቃቱን ሰላባዎች ቁጥር ያስታወቁት የደኅንነት ባለሥልጣናትና የዳስላን ምግብ ቤት ባለቤት ናቸው።

#VOA24
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና

ሶማልያ ዋና ከተማ #ሞቃዲሾ ውስጥ ዛሬ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ፣ በትንሹ 17 ሰዎች #መሞታቸውን የሆስፒታል ምንጮችን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘገበ። የሞቃዲሾ ትልቁ ሆስፒታል ዳይሬክተር ዶ/ር ሞሓመድ ዩሱፍ እንደገለፁት፣ ሌሎች 28 ቁስለኞች ሆስፒታል ገብተዋል። አደጋው የደረሰው አንድ ተጠርጣሪ አጥፍቶ ጠፊ፣ ይጓዝባት የነበረችውን ተሽከርካሪ፣ ሕዝብ በሚበዛበት የሞቃዲሾ አውራ-ጎዳና መጋጠሚያ ላይ በማፈንዳቱ እንደሆነም ተገልጿል። ለፍንዳታው አል-ሻባብ ኃላፊነት መውሰዱንም አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Seaport ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን ጠራች። ሶማሊያ እንደ ራሷ ግዛት በምታያት ሱማሊላንድ እና ኢትዮጵያ መካከል ትላንት በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ እንዳስቆጣት መነገሩ ይታወሳል። ይህን ተከትሎ ከኢትዮጵያ አምባሳደሯን ለምክክር በሚል ጠርታለች። የሀገሪቱ ካቢኔ ዛሬ ማክሰኞ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፦ - የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት) - አፍሪካ ህብረት …
#Update

ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን መጥራቷን ተከትሎ አምባሳደር አብዱላሂ ዋርፋ ወደ #ሞቃዲሾ ማቅናታቸው ተሰምቷል።

በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የሶማሊያ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች በአሁን ሰዓት አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ የተቀመጡ ሲሆን በዚህ ስብሰባ ላይ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል።

ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የወደብ እና የባህር በር ተጠቃሚ ለመሆን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሰላማዊ የሆነና በሰጥቶ መቀበል መርህ የተቃኘ ስምምነት ላይ ለመድረስ ሙከራ ስታደርግ ቆይታለች።

በዚህ ሙከራም ከሶማሊላንድ ጋር በሊዝ የባህር በር ለማግኘት መንገድ የሚጠርግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች።

ስምምነቱ ግን በሶማሊያ መንግስት ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም። ሶማሊያ ራስ ገዟን ሶማሊላንድ እንደ ራሷ አንድ ግዛት ነው የምታያት በመሆኑም መሰል የወደብም ሆነ ማንኛውም ስምምነት በክልል አስተዳደር በኩል ሊፈፀም አይችልም ፤ ይህ ልዓላዊነቴን የሚጥስ ነው እያለች ነው።

@tikvahethiopia
#CPPI #WorldBank

የዓለም ባንክ ከኤስ ኤንድ ፒ ግሎባል ማርኬት ኢንተለጀንስ ጋር የሚያዘጋጀው የኮንቴይነር ወደብ የአፈጻጸም መለኪያ (Container Port Performance Index - CPPI) የ2023 ደረጃ ባሳለፍነው ሳምንት ይፋ አድርጓል።

ይህ መለኪያ ወደቦች የመረከብ አቀባበላቸውንና እንዴት እንደሚያስተናግዱ በአጠቃላይ ያላቸውን የስራ ቅልጥፍና እና አፈጻጸም የሚለካ ነው።

በዚህም ከ409 ወደቦች የራስ ገዟ #ሶማሌላንድ " #በርበራ " ወደብ 106ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የሶማሊያ ፤ " #ሞቃዲሾ " ወደብ ደግሞ 166ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የ " #ጅቡቲ " ወደብ ከመጨረሻ ተርታ 379ኛ ደረጃ ላይ ነው የተቀመጠው።

በዚህ የዓለም ባንክ የአፈጻጸም መለኪያ የበርበራ ወደብ ከሞቃዲሾ እና ጅቡቲ ወደቦች የተሻለ ደረጃ ተሰጥቶታል።

በአጠቃላይ ዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሰጣቸው ከ405 ወደቦች በመጨረሻ ተርታ ማለትም 379 ላይ የተቀመጠው የጅቡቲ ወደብ በሀገሪቱ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል።

የጅቡቲ ወደብ በ2022 ከዓለም የተሰጠው ደረጃ 26ኛ ሲሆን በ2023 መለኪያ 379ኛ ላይ መቀመጡ ጅቡቲን አላስደሰተም።

ሀገሪቱ " የ2023 ደረጃ አሰጣጥ ምክንያታዊነት የጎደለው በመሆኑ ያሳስበናል " ያለች ሲሆን " ምን አይነት ሳይንስ ነው የሚያብራራው በዓለም ደረጃ ከ350 በላይ ነጥብ መጣል ? " ስትል ጠይቃለች።

በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲህ ያለው ደረጃ መሰጠቱ በመለኪያው ላይ የተዓማኒነት ጥያቄ እንደሚያስነሳ ገልጻለች።

ጅቡቲ ፥ " ደረጃ አሰጣጡ ነጻ እና ከተእጽኖ የጸዳ ነው ወይ ? " ስትል ጠይቃ " ለማንኛውም አድሏዊም ሆነ አልሆነ ጅቡቲ ከሰሃራ በታች እና ምስራቅ አፍሪካ ትልቁ እና ቀልጣፋ ማዕከል ናት " ብላለች።

ሙሉ ዶክመንቱን በዚህ ያግኙ ➡️ CPPI 2023

#WorldBank

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia