TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሪፖርት📌የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው አዲስ ሪፖርት በዓለማችን በአማካይ ከ20 ሰዎች ውስጥ አንዱ በአልኮል መጠጥ #እንደሚሞቱ ጠቁሟል።

በፈረንጆቹ 2016 ብቻ ከ3 ሚሊየን በላይ ሰዎች መሞታቸውም በሪፖርቱ ተካቷል።
ከዚህ ውስጥ ከ75 በመቶ የሚበልጡት ወንደች መሆናቸው ተገልጿል።

የአልኮል መጠጡ ለጉዳት በመዳረግ የሚሞቱት ሰዎች 28 በመቶ ሲሆኑ፣ ለምግብ መፈጨት ችግር በመጋለጥ የሚሞቱት 21 በመቶ ያህል ናቸው።

19 በመቶ ያህሉ ደግሞ የአልኮል መጠጡ በሚፈጥረው የልብ ችግር ህይወታቸውን እነደሚያጡ ሪፖርቱ ጠቁሟል።

ቀሪዎቹ ለካንሰር፣ ለቁስ ህመሞች፣ ለአዕምሮ ችግርና ሌሎች በአልኮል ምክንያት ለሚመጡ የጤና መታወክ በማጋለጥ ሰዎችን ለሞት መዳረጋቸውም ተነግሯል።

የአልኮል መጠጥን መጠቀም በዓለም ላይ ከሚገኙ በሽታዎች 5 በመቶ ያህሉ እንዲባባሱ ማድረጉም ነው የተገለጸው።

በዓለም ላይ 237 ሚሊየን ወንዶችና 46 ሴቶች በአልኮል መጠጥ ምክንያት ለአዕምሮ ችግር መዳረጋቸውንም ሪፖርቱ አሳይቷል፤ ለዚህ ጉዳት ከተዳረጉት መካከል አውሮፓውያን ቀዳሚ ሲሆኑ አሜሪካውያን ይከተላሉ።

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር #ቴድሮስ_አድሃኖም ጤናማ ትውልድ ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት ስጋት የደቀነውን የአልኮል መጠጥ አጠቃቀም መዛባት ለመከላከል በትጋት መስራት አለብን ብለዋል።

በዓለም ላይ 2 ነጥብ 3 ቢሊየን ያህል ሰዎች አልኮል ይጠጣሉ። በርካታ ታዳጊዎችም 15 ዓመት ሳይሞላቸው አልኮል መጠጣት እንደሚጀምሩ የዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።

ምንጭ፦ሲኤንኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia