TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert በጋምቤላ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሁለት ቦታዎች እንዲሰጥ ተወሰነ። በጋምቤላ ክልል ሰሞኑን ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ እና በጋምቤላ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እንደሚሰጥ የክልሉ መንግስት አስታውቋል። የክልሉ መንግሥት ፤ " በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ብቻ ሊሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሰሞኑን ተከስቶ በነበረው…
ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓትን ሳያከናውን ቀርቷል።

በክልሉ ባለ የፀጥታ ችግር ምክንያት የ2015 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ በዓል መሰረዙን ዩኒቨርሲቲው ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አረጋግጧል።

የምረቃ በዓሉን ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም ለማድረግ ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም በክልሉ በተከሰተው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የምረቃ ፕሮግራሙ መሰረዙን የተቋሙ ከፍተኛ አመራር ለቲክቫህ ተናግረዋል።

"ተማሪዎቻችንን ለማስመረቅ ተዘጋጅተን ነበር፤ ይሁን እንጂ ባለው የፀጥታ ሁኔታ የምረቃ በዓሉን ማከናወኑ ትርጉም አይኖረውም" ብለዋል ኃላፊው።

የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ አንድ ተማሪ እና አንድ መምህር ባለፈው ሳምንት ህይወታቸው ማለፉን ዩኒቨርሲው ማሳወቁ አይዘነጋም፡፡

ከ650 በላይ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች ትምህርታቸውን በ2015 ዓ.ም በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ማጠናቀቃቸው ተገልጿል። ተመራቂዎቹ አሁን ላይ ጊዚያዊ ዲግሪ (Temporary) እየተሰጣቸው ነው።

በሌላ በኩል ዩኒቨርሲቲው የተመደቡለትን ከ6 ሺህ በላይ የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞችን ከትላንት ጀምሮ እየተቀበለ ይገኛል።

@tikvahuniversity