TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#KenyaElection🇰🇪

የኬንያን ምርጫ እየታዘቡ የሚገኙ #ኢትዮጵያውያን እነማን ናቸው ?

ኬንያ እያካሄደች ያለችውን 5ኛው ዙር ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለመታዘብ ኢትዮጵያውያን ኬንያ ይገኛሉ።

🇪🇹 አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፦

የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃለማርያም ደሳለኝ መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገውን 'ብሬንትረስት ፋውንዴሽን'ን በመወከል ምርጫውን እየታዘቡ ናቸው።

አቶ ኃይለማርያም በሚመሩት ልዑክ ውስጥ እውቁ ኡጋንዳዊ ፖለቲከኛ እና ሙዚቀኛ ቦቢ ዋይን ይገኝበታል።

🇪🇹 ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ፦

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ደግሞ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) ታዛቢ ቡድንን በመምራት ኬንያ ናቸው።

🇪🇹 ፕ/ር መረራ ጉዲና ፦

የተቃዋሚው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ መሪ እና አንጋፋው ፖለቲካኛ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በኬንያ ተገኝተው ምርጫውን እየታዘቡ ይገኛሉ።

🇪🇹 ሌንሳ ቢየና ፦

የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ሌንሳ ቢየና የኤን ዲ አይ/አይ አር አይ (NDI/IRI) ዓለም-አቀፍ ምርጫ ታዛቢ ልኡክ አካል ሆነው በኤልዶሬት ከተማ በዩዜን ጊሹ ካዉንቲ የሚደረገዉን ምርጫ በመታዘብ ላይ ይገኛሉ፡፡

መረጃው ከቢቢሲ እና ከኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ያገኘነው ነው።

@tikvahethiopia