TIKVAH-ETHIOPIA
ጎረቤት ሱዳኖች የጦርነት ጉሰማ ላይ ናቸው ! የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር መጎብኛታቸው ተነግሯል። ቡርሀን ትንሹ ፋሻጋ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኙት አል ዑስራ እና ዋድ ኮሊ አካባቢዎች የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር ነው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ/ም የጎበኙት፡፡…
" የሱዳን ጦር የሚነዛው መረጃ መሰረተ ቢስ ነው " - የኢትዮጵያ 🇪🇹 ሀገር መከላከያ

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የምርኮኞችን አያያዝ ባልጠበቀ መንገድ ወታደሮቼን ገድሏል በሚል የሱዳን ጦር የሚነዛው መረጃ መሰረተ ቢስ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አሳውቋል።

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት በቦታው እንዳልነበርና #የኢትዮጵያን_ግዛት_ዘልቆ የገባው የሱዳን ኃይል ከአካባቢው ሚሊሻዎች ጋር መጋጨቱ ተገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ ሕወሓት ሰሜን ዕዝ ሰራዊት ላይ ጥቃት በፈፀመበት ወቅት የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ግዛት ላይ ወረራ መፈጸሙን አስታውሶ፤ ጦሩ በተለያየ ጊዜ ውስጣዊ ችግሮች ባጋጠሙ ቁጥር በኢትዮጵያ ላይ ትንኮሳዎችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

ሰሞኑ ደግሞ የሱዳን ኃይል ወደ ኢትዮጵያ ግዛት ዘልቆ በመግባት በአካባቢው በነበሩ የኢትዮጵያ ሚሊሻዎች ላይ ጥቃት ማድረሱንና ከሁለቱም ወገን ጉዳት መድረሱን ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል።

ነገር ግን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በስፍራው ባልነበረበት ሁኔታ " ምርኮኞችን ገደለ " በሚል የሱዳን ጦር ክስ ማቅረቡ ተቀባይነት የሌለውና መሰረተ ቢስ መሆኑ አስገንዝቧል።

የደረሰውን ጥቃት በተመለከተ ማጣራት የሚፈልግ አካል ካለ ከሁለቱ ሀገራት መከላከያ ሠራዊት ተወካዮች የተውጣጣ ኮሚቴ ተዋቅሮ እንዲጣራ ለመተባበር የኢትዮጵያ ሠራዊት ዝግጁ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አረጋግጧል።

#ENA

@tikvahethiopia