TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ህመም አጋጥሟቸው ሆስፒታል ይገኛሉ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስም ሆስፒታል በመገኘት ጠይቀዋቸዋል። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሕመም ምክንያት በሆስፒታል ሕክምናቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙትን 4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ…
ፎቶ ፦ አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ህመም አጋጥሟቸው ሆስፒታል እንደሚገኙ ይታወቃል።

ትላንት ቅዳሜ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሆስፒታል በመገኘት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስን መጎብኘታቸው እና እግዚአብሔር ምሕረቱን እንዲልክላቸው ጸሎት በማድረስ መልካም ምኞታቸውን መግለፃቸው ይታወሳል።

በዛሬው ዕለት ደግሞ ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስን ሆስፒታል በመገኘት ጎብኝተዋቸዋል።

በተጨማሪ የኢፌዴሪ ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴም ቅዱስነታቸውን ጎብኝተዋቸዋል። ፕሬዜዳንቷ በቀደመው ጊዜ የቅዱስነታቸው የመንፈስ ቅዱስ ልጅ መሆናቸውን ገልፀው በቶሎ ድነው ከሆስፒታል እንዲወጡ ምኞታቸውን ገልፀዋል።

ቅዱስነታቸው በሀሌሉያ ሆስፒታል በመደበኛ ክል ህክምናቸውን እየተከታተሉ ሲሆን ወደ ፅኑ ህሙማን ክፍል አለመግባታቸው ተገልጿል።

@tikvahethiopia