TIKVAH-ETHIOPIA
#Egypt #Djibouti ኢማኤል ኦመር ጌሌ ግብፅ ገብተዋል። የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በተደረገላቸው ግብዣ ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ትላንት ለሊት ግብፅ ገብተዋል። ፕሬዜዳንቱ ካይሮ ኤርፖርት ሲደርሱ አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ናቸው የተቀበሏቸው። በዛው ዕለት ሁለቱ መሪዎች ስብሰባ የሚኖራቸው ሲሆን በሁለትዮሽ ጉዳዮቻቸውና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ…
#Update

ትላንትና ለሊት ግብፅ ፣ ካይሮ የገቡት የጅቡቲው ፕሬዜዳንት እና የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ዛሬ ውይይት አድርገዋል።

በውይይታቸው ላይ ሀገራችን #ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገናባችው ስላለው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መነሳቱ ታውቋል።

ከውይይቱ በኃላ በተሰጠ መግለጫ ላይ አብዱል ፈታህ አልሲሲ ሀገራቸው ግብፅ አሁንም በህዳሴ ግድብ ላይ አስገዳጅ ስምምነት እንደምትፈልግ ከዚህ በፊት ሲናገሩት የነበረውን ንግግር አንስተው ተናግረዋል።

የመሪዎቹ ውይይት ከሀገራችን የህዳሴ ግድብ በተጨማሪም በቀይ ባህር እና በአፍሪካ ሰላም እና ደህንነት በተለይም የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።

የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠከቀር ያለመም ውይይት አድርገዋል።

የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌህ ከፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ጋር የተደረገው ውይይት ገንቢ እና ፍሬያማ መሆናቸውን ገልጸው፣ “የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን በሁሉም ደረጃ ማጠናከርና ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ” መምከራቸውን ስለመናግረራቸውን AFP ዘግቧል።

@tikvahethiopia