TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Egypt #Djibouti

ኢማኤል ኦመር ጌሌ ግብፅ ገብተዋል።

የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በተደረገላቸው ግብዣ ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ትላንት ለሊት ግብፅ ገብተዋል።

ፕሬዜዳንቱ ካይሮ ኤርፖርት ሲደርሱ አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ናቸው የተቀበሏቸው።

በዛው ዕለት ሁለቱ መሪዎች ስብሰባ የሚኖራቸው ሲሆን በሁለትዮሽ ጉዳዮቻቸውና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ ተብሏል።

ፎቶ፦ የጅቡቲ ፕሬዜዳንት (ኢሳማኤል ኦመር ጌሌ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU2022Summit " ... ህብረቱ የኢትዮጵያ ቀውስ በሰላማዊ መንገድ እንዲቋጭ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ ቀጥሏል " - አምባሳደር ባንኮሌ አዴኦዬ የአፍሪካ ህብረት ለኢትዮጵያ ግጭት ሰላማዊ መፍትሔ ለማፈላለግ ከአህጉሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ተጨማሪ ባለሙያዎችን ወደ ስራ እንደሚያስገባ አስታውቋል። የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዴኦዬ ፤ በአሁኑ ወቅት የአፍሪካ ህብረት…
#Update

ኦባሳንጆ ኮምቦልቻ ገብተዋል።

የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕከተኛ ኦሊሴንጎን አባሳንጆ ዛሬ ኮምቦልቻ ገብተዋል።

በትላንትናው ዕለት የሰላም እና ጸጥታ ምክር ቤት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዴኦዬ ፤ የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቀውስ በሰላማዊ መንገድ እንዲቋጭ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ መቀጠሉን በመግለፅ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በአማራ እና በአፋር ክልሎች በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ጉብኝት እንደሚያደርጉ ማሳወቃቸው አይዘነጋም።

ዛሬ ኮምቦልቻ የገቡት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ በከተማው ያለ የጅምላ መቃብር ስፍራ እና የወደሙ ተቋማትን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

@tikvahethiopia
#Amhara

የአማራ ክልል መንግስት ፋኖን ሆነ ሌሎች አደረጃጀቶች በሚመለከት አቋሙን እንዳልየቀረ አስታውቋል።

መንግስት ፋኖንም ሆነ ሌሎች የፀጥታ አደረጃጀቶችን በሚመለከተ ኢመደበኛ አደራጀጀቶችን ለማፍረስ ይፈልጋል ተብሎ ከሰሞኑ የተናፈሰው ወሬ የመንግስት አቋም አይደለም ሲል የክልሉ መንግስት አስታውቋል።

መነሻቸው ምን እንደሆነ ለማይታወቅ በየጊዜው ለሚቀርቡ አሉባልታዎችና ያልተጨበጡ ወሬዎች ምላሽ መስጠት አስፈላጊ አለመሆኑን የገለጸው የክልሉ መንግሥት፣ ፋኖን በሚመለከት አቋሙ ከዚህ በፊት እንደነበረው መሆኑን ገልጿል።

የአማራ ክልል የኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ጦርነቱ ገና አለማለቁንና ትግሉ መቀጠሉን ገልፀው" ለክልሉንና የአገር ህልውና ለመታደግ የተሳተፉ ኃይሎች በሙሉ ዕውቅና እንሰጣለን" ብለዋል፡፡

የመንግስት አቋም በመርህ ላይ የተመሠረተ መሆኑን በመግለጭ "በህልውና ትግሉ ወቅት የተፈጸሙ ችግሮች ካሉ እርማት ይደረጋል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ትናንት ያሞገስነውን ኃይል ዛሬ ኃጢያተኛ የምናደርግ ሰዎች አይደለንም" ሲሉ ገልፀዋል።

መንግስት የፋኖ አደረጃጀትን ለማፍረስ አቋም ይዟል በሚል ለሚነሳው ጉዳይ አቶ ግዛቸው በክልሉ መንግስትም ሆነ በፌዴራል ደረጃ ይህን መሰል አቋም አለመንፀባረቁን ተናግረዋል፡፡

"ነገርየው ዩቲዩበሮች፣ አክቲቪስቶችና ተንታኝ ነኝ ባዮች የፈጠሩት ተራ አሉባልታ ነው" ሲሉ ገልፀዋል።

የፋኖ አደራጅና መሪ ከሆኑት አንዱ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ፥ ጉዳዩን ለማጥራት ከመንግሥት ጋር ውይይት መጀመሩን ተናግረዋል።

መቶ አለቃ፥ "ከመንግሥት ጋር ንግግር ጀምረናል፣ ስንጨርስ የደረስንበትን ለሕዝብ እናሳውቃለን፤ ጉዳዩ ከየት እንደመጣና መነሻው ምን እንደሆነ በውይይት ይጠራል" ብለዋል፡፡

ያንብቡ : telegra.ph/RP-02-07

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#SomaliPP

በሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ምን ተፈጠረ ? ፓርቲው ለሁለት ተከፍሏል ?

የሶማሌ ክልል የኮሚኒኬሽን ምክትል ኃላፊ አቶ መሀመድ ሮብሌ ፦

" ... ከዚህ በፊት በተለያዩ ቦታ ተሰጥቷቸው በክልሉ በቢሮ ኃላፊ እና በምክትል ኃላፊነት ደረጃ የነበሩና ከዛ በኃላ በነበሩ ግድፈቶች እና ድክመቶች ስራቸውን በትክክል አለመስራት ፣ በሙስና፣ በተለያዩ ምክንያቶች ከስልጣን የተባረሩ ሰዎች ናቸው።

ተሰባስበው Issue ለመፍጠር ሲሉ ነው እንጂ በፓርቲው መሃል ምንም የተፈጠረ ችግር የለም።

እነዚህ Alredy ከሲስተም የወጡ ሰዎች ናቸው። ምናልባት አንዳንድ በትክክለኛ መንገድ ተገምግመው ያልተባረሩ ሰዎች እዛ ውስጥ ሊኖሩ ይችላሉ ፤ ሌላው ግን በትክክል ከሲስተም የወጡና ህብረተሰቡን ማገልገል ሳይችሉ ፣ የተሰጣቸውን ስራ መስራት ሳይችሉ ቀይርተው የተባረሩ ናቸው። "

የሶማሌ ክልል የብልፅግና ፓርቲ የፅ/ቤት ኃላፊ እንጂነር መሀመድ ሻሌ ፦

" ... እኛም በሶሻል ሚዲያ ያየነው ነገር አለ። የነበረ ነገር ግን ከለውጡ ወዲህ የተለያዩ እርምጃዎች ሲወሰዱ ነበር ከስነምግባር እና ከሙስና ጋር በተያያዘ በዚህም ከስልጣን የተነሱ ሰዎች አሉ።

ትላንትና መግለጫ አውጥተዋል ተብለው በሶሻል ሚዲያ ያየኃቸው ሰዎች ነበሩ። አብዛኛው የካቢኔ አባል የክልሉ ማዕከላዊ ኮሚቴ ያኔ የለውጡ ጅምር አካባቢ የነበሩ ሰዎች ናቸው ነገር ግን በስራ ከኃላፊነት እንዲነሱ እና እንዲታገዱ ተደርጎ ነበር። ከአንድ አመት ተኩል ይሆናል።

አንዳንዶቹ የ #ኢዜማ እጩ ነበሩ የምርጫ አካባቢ፤ አሁን ትላንት ብቻ ነው በድንገት ያየናቸው እኛ ፓርቲ አባል ነን ብለው ፤ ከእኛ ጋር ከታገዱ እና ከስራ ከተነሱ ግማሹ ሁለት ዓመት ሆኖታል ግማሹ አንድ አመት ተኩል ፣ አንዳንዶቹ የሌላ ፓርቲ ዕጩ የነበሩ ናቸው።

ጉባኤ ላይ ውሳኔ የሚጠብቁ አሉ፤ እገዳ የተጣለባቸውም አሉ፤ አንዳንዶቹ ግን ጭራሽ አይመለከቱንም የኢዜማ እጩ የነበሩትን ዛሬ ላይ አባል ነው አይደለም ማለት ተገቢም አይመስለኝም "

አቶ ሲራጅ አደን (የሶማሌ ክልል የብልፅግና ፓርቲ አባል ነኝ ያሉ ሲሆን ፓርቲው ለሁለት መከፈሉን ይናገራሉ ) ፦

" የተፈጠረው የፓርቲው ለሁለት ተከፍሏል። የዚህ ምክንያት ያለ ግምገማ እና በብዛት በዝምድና እና በጋብቻ የተሳሰረ ስለሆነ ብዙ ጊዜ ህግ እና ደንብ አይከተልም በዛ ምክንያት ፓርቲው በሁለት በኩል ተከፍሏል።

አንድ ሰው ላይ በፓርቲ እርምጃ መውሰድ የሚቻለው በህግ እና ደንብ አሰራሩ ነው። ያለ ጉባኤ አንድ የአስፈፃሚ ኮሚቴ ወይም አንድ የማዕከላዊ ኮሚቴ አንድ ሰው ውስኖ ከህግ ውጭ አንድን ሰው ከፓርቲ ውጭ ነው ማለት አይችልም በጉባኤ ነው የሚችለው።

የተፈጠረው የ12 አባላት የፓርቲው ማሀከለኛ እና ሁለት የአስፈፃሚ ኮሚቴ ለፌዴራል የፓርቲው ፅ/ቤት አዲስ አበባ ደብዳቤ በመፃፍ ጣልቃ እንዲገባ ጠይቋል።

... ረብሻ አይደለም ህግ እና ደንቡን መከተል ነው። "

NB : የሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ዛሬ መግለጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

ሁሉም አካላት ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ከሰጡት ቃል የተወሰደ።

@tikvahethiopia
" እኔ የምመርጠው እኔ ያገኘሁትን ህዝቦቼ በጥቂቱም ቢሆን እንዲያገኙ ነው " - ሳዲዮ ማኔ

የሊቨርፑል ሴኔጋላዊው 🇸🇳 የፊት መስመር ተጫዋች ሳዲዮ ማኔ ከውድ ቀሳቁሶችን ከመግዛት ለሀገሪቱ ሰዎች እርዳታን ማድረግ ምርጫው እንደሆነ ይገልጻል።

ሳዲዮ ማኔ ፦

" ... ለምን አስር ፌራሪዎችን ፣ ሀያ ውድ ሰዓቶቾን አልያም የግል አውሮፕላኖችን እመኛለው።

ትምህርት ቤቶችን፣ ስታዲየሞችን እገነባለው፤ እኛ አልባሳትን እና ምግቦችን በድህነት ላይ ለሚገኙ ሰዎች መስጠት አለብን።

እኔ የምመርጠው እኔ ያገኘሁትን ህዝቦቼ በጥቂቱም ቢሆን እንዲያገኝ ነው "

የሴኔጋላዊውን ኮከብ ሳድዮ ማኔን ህይወት ውጣ ውረድ ጉዞ ለማንበብ https://publielectoral.lat/tikvahethsport/25770

More : @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoH የጤና ባለሞያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ከታህሳስ 21 እስከ ታህሳስ 27 ድረስ ይሰጣል። በህክምና ፣ ነርሲንግ ፣ ጤና መኮንን ፣ ፋርማሲ ፣ ሜዲካል ላብራቶሪ ቴክኖሎጂ፣ ሚድዋይፈሪ፣ አንስቴዥያ፣ ዴንታል ሜድስን እና ሜዲካል ራዲዮሎጂ ቴክኖሎጂ ሙያዎች ተመርቀው የጤና ሚኒስቴር የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ ለተመዘገቡ የጤና ባለሙያዎች ፈተናው የሚሰጠው ከታህሳስ 21-27/2014 ዓ.ም…
#Update

የፈተና ውጤታችሁን ከነገ ጀምሮ መመልከት ትችላላችሁ።

በህክምና /Medicine/ ሙያ የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች የፈተናው ውጤት ከነገ ጀምሮ መመልከት ይቻላል።

ከታህሳስ 21-27/2014 ዓ.ም የተሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ የህክምና /Medicine/ ተመዛኞች ከየካቲት 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በውጤታቸው ላይ ቅሬታ ያላቸው ተመዛኞች ከየካቲት 1 ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0118275936/37 በመደወል ወይም በኢሜይል hpcald@moh.gov.et ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

ጤና ሚኒስቴር በሌሎች የሙያ ዘርፎች ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ውጤት በቅርብ ቀን ውስጥ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA😷

የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦

▪️ የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 👉 6,327
▪️ ቫይረሱ የተገኘባቸው 👉 138
▪️ ህይወታቸው ያለፈ 👉 10
▪️ ከበሽታው ያገገሙ 👉 3,371
▪️ ፅኑ ታማሚዎች 👉 197

በኢትዮጵያ ውስጥ የ ኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጊዜ አንስቶ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 466,677 የደረሰ ሲሆን ከነዚህ መካከል 7,373 ህይወታቸው አልፏል ፤ 403,319 ከበሽታው አገግመዋል።

በአሁን ሰዓት ቫይረሱ ያለባቸው 54,983 ሰዎች ናቸው።

በኢትዮጵያ ክትባት መሰጠት ከጀመረ አንስቶ የተከተቡ ዜጎች 9,372,192 ደርሰዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ : ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫን ተረክባለች። ሴኔጋል የአፍሪካን ዋንጫ ካነሱ ሀገራት መካከል ስሟን አስመዝግባለች። ዋንጫውን ይዛ ወደ ሀገሯ ስትገባ ደግሞ እጅግ ደማቅ የሆነ አቀባበል እንደሚደረግላት ይጠበቃል። 🇸🇳 C H A M P I O N S O F A F R I C A 🏆 #AFCON2021 በዚህ ተደምድሟል። @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Senegal , #Dakar📍

ሴኔጋል ድል አድራጊውን ብሄራዊ ቡድን ተቀብላለች።

የ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ የሆነው የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን የሴኔጋል ርዕሰ መዲና ዳካር ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

የሴኔጋል ፕሬዜዳንት ማኪ ሳልና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ኤርፖርት በመገኘት ቡድኑን ተቀብለዋል።

የዳካር ነዋሪዎችም ግልብጥ ብለው አደባባይ በመውጣት ለድል አድራጊው ብሄራዊ ቡድናቸው ደማቅ አቀባበል አድርገዋል።

@tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
#Egypt #Djibouti ኢማኤል ኦመር ጌሌ ግብፅ ገብተዋል። የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌ ከፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በተደረገላቸው ግብዣ ለሁለት ቀን የስራ ጉብኝት ትላንት ለሊት ግብፅ ገብተዋል። ፕሬዜዳንቱ ካይሮ ኤርፖርት ሲደርሱ አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ናቸው የተቀበሏቸው። በዛው ዕለት ሁለቱ መሪዎች ስብሰባ የሚኖራቸው ሲሆን በሁለትዮሽ ጉዳዮቻቸውና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ…
#Update

ትላንትና ለሊት ግብፅ ፣ ካይሮ የገቡት የጅቡቲው ፕሬዜዳንት እና የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ዛሬ ውይይት አድርገዋል።

በውይይታቸው ላይ ሀገራችን #ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገናባችው ስላለው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መነሳቱ ታውቋል።

ከውይይቱ በኃላ በተሰጠ መግለጫ ላይ አብዱል ፈታህ አልሲሲ ሀገራቸው ግብፅ አሁንም በህዳሴ ግድብ ላይ አስገዳጅ ስምምነት እንደምትፈልግ ከዚህ በፊት ሲናገሩት የነበረውን ንግግር አንስተው ተናግረዋል።

የመሪዎቹ ውይይት ከሀገራችን የህዳሴ ግድብ በተጨማሪም በቀይ ባህር እና በአፍሪካ ሰላም እና ደህንነት በተለይም የአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል።

የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠከቀር ያለመም ውይይት አድርገዋል።

የጅቡቲ ፕሬዜዳንት ኢስማኤል ኦመር ጌሌህ ከፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ጋር የተደረገው ውይይት ገንቢ እና ፍሬያማ መሆናቸውን ገልጸው፣ “የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን በሁሉም ደረጃ ማጠናከርና ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ” መምከራቸውን ስለመናግረራቸውን AFP ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Walta💻

ከ864 ሺህ በላይ ተከታይ ያለው የዋልታ የፌስቡክ ገፅ መጠለፉን ለመመልከት ተችሏል።

የፌስቡክ ገፁ በክሪፕቶ ከረንሲ ጠላፊዎች እጅ እንደገባ የሚፃፉት ኮዶች እንደሚያመላክቱ የዘርፉን ባለሞያ ዋቢ አድርጎ ኢትዮጵያ ቼክ አስነብቧል።

የአክስዮን እና ክሪፕቶ ከረንሲ የሚገበያይ ነጋዴ የሆነው አብነት ተፈራ፥ " እየጠየቁ ያሉት የክሪፕቶ ከረንሲ ቲተር (Tether) ነው። ቴተር ማለት ወደ አሜሪካ ዶላር የሚመነዘር እና የሚተመን መጠን ያለው ሲሆን ስሌቱም 1 $. 5000 USDT = 5000$ ነው። " ብሏል።

አክሎም " በስተመጨረሻ የሚታየው ረጅም ቁጥር ደግሞ ኤተሪየም ዋሌት (Ethereum wallet) አድራሻ ነው፣ በህግ አስከባሪዎች እንዳይታወቁ ደግሞ አድራሻውን እየቁያየሩት ይገኛል" ሲል ለ ኢትዮጵያ ቼክ አስረድቷል።

ገፁን በቁጥጥር ስር ያዋሉት ጠላፊዎች የገፁን አድራሻ የቀየሩት ሲሆን የተለያዩ መልዕክቶችንም እያስተላለፉ ይገኛሉ። የገፁ ፕሮፋይል ፒክቸርም ተነስቷል።

ዋልታ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬት በበኩሉ ሕጋዊ የፌስቡክ ገጹ የቴክኒክ ችግር እንደገጠመው ገልጿል።

ድርጅቱ በፌስቡክ ገፁ ላይ የገጠመውን የቴክኒክ ችግር ለመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን በመግለፅ ችግሩ መፈታቱን አስከሚያስታውቅ ድረስ በፌስቡክ ገፁ የሚለጠፉ ማናቸውም መልዕክቶች ከተቋሙ ዕውቅና ውጭ መሆናቸውን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
መግለጫ ፦

" መንግስት በሴቶች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለማስቆም መስራት አለበት "

- የኢትዮጵያ ሴት ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥምረት
- የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶችት ተሟጋቾች ማዕከል
- የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ
- የመብቶችና ዲሞክራሲ እድገት ማዕከል
- የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሚያ ሴቶች ማህበር
- ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ
- የስቄ የሴቶች ልማት ማህበር
- ምዥዥጎ ሎካ የሴቶች ልማት ማህበር
- ሴታዊት ንቅናቄ፣
- ትምራን ኢትዮጵያ፣
- ሔልዝ ኤንድ ሆልነስ ኢትዮጵያ በሀገራችን በሴቶች ላይ የሚፈፀም ግድያና ጾታ መሰረት ያደረገ ጥቃት መባባስ በእጅጉ እንዳሳሰባቸው በጋራ ባወጡት መግለጫ አሳውቀዋል።

የቅርብ ጊዜው የሰብል ንጉሴ እና የጸገሬዳ ግርማይ ጉዳይ ሁሉንም በእጅጉ ካሳዘኑ በርካታ ኢሰብአዊ ወንጀሎች መካከል የሚጠቀሱ መሆኑን ገልፀዋል።

ከጊዜ ወደ ጊዜ ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እየበዙ መምጣታቸውን አስገንዝበዋል።

ከላይ የተዘረዘሩት ማህበራት እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ፍትህ ሚኒስቴር የእነሰብለ ንጉሴ እና የፅጌረዳ ግርማይ የክስ ሂደት በአግባቡ እንዲሄድ ፤ ጉዳዩን በመመርመርም ፍትህን እንዲያረጋግጥ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት የእንደዚህ አይነት ጥቃቶች መበራከትን ከግምት ውስጥ በማስገባት ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ህግጋቶችን በአስቸኳይ እንዲያስተካክልም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ዜጎች ሁሉ እነዚህን የጥቃት ድርጊቶች እንዲያወግዙም ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ሚዲያዎች መሰል ድርጊቶችን እንዲያወግዙ እና ለተጎጂዎች ድምጽ እንዲሆኑ አሳስበዋል።

(ሙሉ መግለጫቸው ከላይ ተያይዟል - ያንብቡ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray , #Mekelle 📍 አሚና መሐመድ ትግራይ ክልልን ጎብኝተዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሐመድ የተመራ ልዑክ ዛሬ በትግራይ ክልል መቐለ ጉብኝት አድርጓል። የልዑካን ቡድኑ በመቐለ ከተማ ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታልን ተዘዋውሮ ጎብኝቷል ፤ የጤና ባለሞያዎችን አነጋግሯል። ከዚህ በተጨማሪም በመቐለ የሚገኙ በጦርነት የተፈናቀሉ ወገኖች የሚገኙባቸውን ካምፖች…
ስለ አሚና መሐመድ የአማራ እና የትግራይ ክልል ጉብኝት ምን ተባለ ?

የተባበሩት መንግሥታቱ ድርጅት ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሐመድ በጦርነቱ የተጎዱ የአማራና የትግራይ ክልል ከተሞችን ጎብኝተዋል። እንዲሁም ከክልል አመራሮች ጋር ተገናኝተዋል።

አሚና ባለፈው እሁድ በአማራ ክልል ኮምቦልቻን የጎበኙ ሲሆን ጦርነቱ በሕዝቡ በተለይ በሴቶችና በህፃናት ላይ ያደረሰውን አስከፊ ጉዳት ማየታቸውን ተመድ አስታውቋል።

በሆስፒታሎች፣ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በገበያ ስፍራዎች እና በሌሎች አካባቢዎች ላይ የደረሰውን ዘረፋና ውድመት የተመለከቱ ሲሆን የአማራ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ሌሎችንም ባለሥልጣናትን አግኝተዋል።

ከኮምቦልቻ ጉብኝታቸው በኋላ ጦርነቱ ብዙ ያስከፈለ መሆኑን ገልጸው ሰላም ብቸኛ አማራጭ እንደሆነ ተናግረዋል "የኢትዮጵያን ሕዝብ ሰላም እንዲያገኝ መርዳት አለብን" ሲሉም ተናግረዋል።

ከኮምቦልቻ ቀጥለቅ ወደ ትግራይ ክልል፣ መቐለ ያቀኑት አሚና በጦርነቱ በሴቶችና በህፃናት ላይ ያደረሰውን አስከፊ ገፅታ ተመልክተዋል።

ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና ለኢትዮጵያውን የሚያመጣውን እፎይታን በተመለከተ ከዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር መወያየታቸው ንተመድ ገልጿል።

አሚና በተመድ የሚደገፈውንና ከወሲባዊ ጥቃት የተረፉ ሴቶችን ጨምሮ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ የሚያደርገውን የአይደር ሆስፒታልን ጎብኝተዋል።

" በግጭት ውስጥ አሸናፊዎች እንደሌሉ " በመጥቀስ ወሲባዊ ጥቃት የተረፉ ሴቶቹ ታሪኮች ሊነገሩ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

በሁለቱ ክልሎች ከሴቶች እንዲሁም ከተማሪዎች ጋር ባደረጉት ቆይታ የተመድ ወሲባዊ እንዲሁም ፆታን መሰረት ላደረጉ ጥቃቶችን እንደማይታገስ አፅንኦት በመስጠት ተናግረዋል።

አሚና ወሲባዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች አጋርነታቸውን ገልፀዋል።

በጦርነቱ ምክንያት በሴቶች ላይ የደረሰውን ግፍ እና በደል እንዲሁም አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ለማቃለል ተመድ መፍትሄ በማፈላለግ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ሴቶች ካለባቸው ህመም እንዲፈወሱ በተሃድሶ እና በመልሶ ማቋቋም ሥራዎች ውስጥ እንዲካተቱም አመራሮቹን አሳስበዋል።

በተጨማሪ ተመድ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገውን የሰላም ጥረትም ይደግፋል ብለዋል።

#UnitedNations

@tikvahethiopia
#MoE

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር) ፦

• የፈተና መሰረቅ ከግለሰብ ይልቅ ተቋማዊ እየሆነ በመምጣቱ ፤ በአጠቃላይ የደረሰብን የሞራል ክስረት ከፍተኛ ነው።

• የእኔ ክልል ተማሪዎች ማለፍ አለባቸው በሚል በተቋም ደረጃ የፈተና ወረቀቶችን በመስረቅና መልስ በመስጠት ጭምር ተባባሪ የሆኑ አመራሮች መኖራቸው የትምህርት ሲስተሙ ጥራት ተዓማኒነት ከፍተኛ ጥያቄ ዉስጥ ገብቷል።

• ግማሹ ለፍቶ ጥሮ ዉጤት እየያዘ ፣ ሌላዉ ደግሞ ከድግሪ ፋብሪካዎች ድግሪ እየተቀበለ የሚያልፍበት ሁኔታ ካለ ችግሩ የተወሰኑ ሰዎች ማለፍ ሳይሆን ፣ ችግሩ የትምህርት ጥራቱ ላይ ነዉ።

• ፈተና የሰዎችን ክህሎት እና ታታሪነት መለኪያ መሆኑ ቀርቶ ተሰርቆ ና መልስ ተሰጥቶ የሚመጣ ዉጤት ምዘና አያሟላም፣ ተዓማኒነት አይኖረዉም።

• የትምህርት ተቋማት ምዘና ተደርጎባቸዉ ሰርተፊኬት ይስጡ በሚባልበት ሁኔታ በተለይ ለግል ትምህርት ቤቶች የስራ ሰርተፊኬት የሚሰጠዉ በችሎታቸዉ ሳይሆን በጉቦ ከሆነ ሲስተሙ ፈርሷል ይህንንም ሁላችንም ነው የምናዉቀዉ ነገርግን ፊትለፊት ስለማንነጋገርበት ስር የሰደደ መፍትሄ ልንፈልግለት ያልቻልነዉ ጉዳይ ነዉ።

• የትምህርት ስርዓቱን ተዓማኒነት ጥያቄ ዉስጥ የሚከት አካሄድ በጣም ተንሰራፍቷል።

• የትምህርት ስርዓቱን ለማሻሻል እንደዚህ ያሉ አሰራሮችን ማስቆም እና የሲስተሙን ተዓማኒነት ችግር ዉስጥ የሚከቱ ጉዳዮችን ከስር መሰረታቸዉ መፍታት አለብን።

[ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ለህዝብ ተዋካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ነው ] - ከኢትዮ ኤፍ ኤም

@tikvahethiopia
#ችሎት

እነ አቶ አብዲ ኢሌ ተቃውሞ አሰሙ።

ዛሬ ፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የፀረ-ሽብር እና የህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የቀረቡት የቀድሞ የሱማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር (አብዲ ኢሌ) ጨምሮ 17 ተከሳሾች ተቃውሞ አሰምተዋል።

እነ አቶ አብዲ ኢሌ ከኛ ጋር ታስረው የነበሩት እስረኞች ተፈተው እኛ የምንታሰርበት ምክንያት የለም ሲሉ ነው ተቃውሞ ያሰሙት።

አቶ አብዲ መሀመድ እጃቸውን በማንሳት ይህን ተናግረዋል ፦

" ከዚህ በኋላ ፍርድ ቤት አንቀርብም እኛ ከስር ከተፈቱ ግለሰቦች የተለየ ምንም ወንጀል አልፈጸምንም። ስለዚህ ሌሎች ዕስረኞች ተፈተው እኛ ታስረን ፍርድ ቤት የምንቀርብበት ምክንያት የለም።

ከአማራ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፣ ከትግራይ እና ከሌሎችም ከተፈጸመው ወንጀል የኛ በምን ይለያል ?

ግድያ በተፈጸመበት ሁኔታ ሌሎች ሳይጠየቁ እኛ ብቻ የምንታሰርበት ጉዳይ የለም። ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ እኛ ፍርድ ቤት አንቀርብም። ፍርድ ቤቱ የራሱን ውሳኔ ይስጥበት "

ከሳሽ አቃቤ ህግ ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ አስተያየት ይስጥበት እና ክርክሩ ይቀጥል ሲል ችሎቱን ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ ከእስር የተፈቱ እስረኞችን ክስ ያቋረጠው ፍትህ ሚኒስቴር መሆኑን ገልጿል።

አስተያየታቸዎውን ለፍትህ ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚችሉ የገለጸው ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ መርምሮ ተገቢውን ትዛዝ ለመስጠት ለፊታችን ሀሙስ የካቲት 3ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።

(የመረጃ ባለቤት ፦ ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ)

ያንብቡ : https://telegra.ph/Abdi-Muhamud-Omer-02-08
#EthiopianCatholicChurch

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተከርስቲያን የማህበራዊና ልማት ኮሚሽን የሴቶችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል በርካታ ስራዎችን ታከናውናለች፡፡

በዚህም በአዲስ አበባ ሀገረስብከት የልማት ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር “የከፍተኛ ትምህርት ተመራቂ ሴቶች የስራ ተወዳዳሪነትን ማሻሻል ለተሻለ የስራ እድል ተጠቃሚነት” በሚል መነሻ ሃሳብ ጥናታዊ ፕሮጅክት ለማካሄድ በሀገር አቀፍ ደረጃ ማቀዷን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቃለች።

የጥናቱ ዋነኛው ዓላማ ምሩቃን ሴቶችን በስራ ዝግጁነት ስልጠና በማሰልጠን የስራ እድል መረጃዎችን በማቅረብ እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በመስጠት እና በማብቃት የስራ ተወዳዳሪነታቸውን መጨመር መሆኑ ተገልጿል።

ሂደቱ ለሴቶች ተቃሚነት ያለውን ሚና በጥናት በማስረዳት ለፖሊሲ ግብዓት በመሆን ያገለግላል ተብሏል። ጥናቱ ከሚካሄድባቸው ስፍራዎቸ የአዲስ አበባ ከተማ አንዱና ዋነኛው መሆኑ ተገልጿል

ጥናታዊ ፕሮጀክቱ በአ/አ ከ2009 ጅምሮ እስከ 2013 ዓ.ም ባለው የትምህርት ዘመን ከታወቀ ዩኒቨርስቲዎች ተመርቀው መደበኛ የሥራ ዕድል ያላገኙ 662 ሴት የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎችን ያሳትፋል፡፡

በመቀጠልም ይህ ፕሮጀክት ለ 441 ሴት ምሩቃን በግልጽ ሂደት ተመርጠው የስልጠናዎች እና የሥራ እድል መረጃ በመስጠት ተጨማሪ ድጋፎች ያደርጋል፡፡

( ዝርዝር መስፈርቶች ፣ የመመዝገቢያ ቦታ እና ተጨማሪ መረጃዎች ከላይ ተያይዟል )

@tikvahethiopia
የ245 ሺህ ብር ሽልማት ያሸነፉት ተማሪዎች👏

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኬሚካል ምህንድስና ሴት ተማሪዎች የፍራፍሬ እና ሌሎች የዕፀዋት ተረፈ ምርቶችን በመጠቀም ለወረቀት መስሪያ የሚሆን “ፐልፕ” በማምረት በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጀው የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ የ245 ሺህ ብር አሸነፊ ሆኑ፡፡

ተማሪዎቹ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ የማይመረተውን ፐልፕ የተሰኘውን ለወረቀት ማምረት ስራ የሚውል ግብዓት በማምረታቸው ነው ውድድሩን ያሸነፉት፡፡

የተማሪዎቹ የፈጠራ ስራ ፕሮጀክት በገንዘብ ቢደገፍና ወደ ተግባር ቢለወጥ ቆሻሻን መልሶ በመጠቀም ከሚሰጠው ፋይዳ በተጨማሪም የአከባቢ ንፅህናን በመጠበቅ ደረጃ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia