#Bahirdar : በባህርዳር ከተማ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህገ-ወጥ ሽጉጥ እንዲሁም የብሬን፣ የክላሸና የሽጉጥ ጥይቶች በቁጥጥር ስር ዋለ።

በባህር ዳር ከተማ ልዩ ቦታው ዳግማዊ ምንሊክ ክፍለ ከተማ ማርዘነብ ቀበሌ በተባለው ስፍራ በአንድ ግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ፦
- 51 ትልቁ ቱርክ ሰራሽ ህገ-ወጥ ሽጉጥ፣
- 2ሺ 1መቶ የብሬን ጥይት፣
- 69 የክላሽ ጥይት እንዲሁም 222 የሽጉጥ ጥይቶች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋሉን የባህር ዳር ከተማ ፖሊስ አሳውቋል።

የባህር ዳር ፖሊስ ፥ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያው በቁጥጥር ስር የዋለው የአማራ ክልል ፖሊስ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንዲሁም ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በትብብር መሆኑን ገልጿል።

የባህር ዳር ፖሊስ 9ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ንብረቱ ሞት ፥ ህብረተሰቡ ከዚህ መሰል ህገ-ወጥ ድርጊት እንዲቆጠብ ያሳሰቡ ሲሆን "ህገ-ወጥ ድርጊት ፈፃሚ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በምናውልበት ጊዜ ህዝቡ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን በመሆን ትብብሩን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል" ሲሉ ጥሪ አስተላፈዋል።

@tikvahethiopia