#አስቸኳይ

የሳዑዲ አረቢያ የፀጥታ አስከባሪ አካላት በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነና ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፎ ነበር።

የሳዑዲ ፀጥታ ኃይሎች በሰሩት ኦፕሬሽን ተይዘው በሹሜሲ የማቆያ ጣብያ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የውሃ የምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች እጥረት እንዳጋጠማቸው ተሰምቷል።

በመሆኑም:-

1ኛ. ከ10 ቀን እስከ 3 ዓመት ዕድሜ ላላቸው ህፃናት የሚሆን ወተት

2ኛ. ከ1 ቁጥር እስከ 5 ቁጥር የሆኑ የህፃናት ዳይፐር/ሃፋዛ/

3ኛ. ለታዳጊ ህፃናት እና ለአዋቂዎች የሚሆኑ ደረቅ ምግቦች

4ኛ. ለሴቶች እና ለሕፃናት የሚሆኑ የመፀዳጃ ቁሳቁሶች በተለይ ዋይፕ እና ሞዴስ

5ኛ. የሚጠጣ ውሃ እጥረት ያጋጠመ በመሆኑ ዜጎቻችን ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል።

ዕርዳታ ማድረግ የምትፈልጉ ግለሰቦች/ አደረጃጀቶች በጄዳ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ (ኮሚዩኒቲ) የስራ ኃላፊነቱን ወስዶ እንቅስቃሴ የጀመረ በመሆኑ ዕርዳታችሁን በኮሚኒቲ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 1 ማድረስ እንደሚቻል በጄዳ የሚገኘው ቆንስላ ፅ/ቤት ዛሬ ማምሻውን ገልጿል።

ይህ መልዕክት የደረሳችሁ ጅዳ አካባቢ የምትገኙ የቲክቫህ አባላት በመሉ የምትችሉትን ሁሉ ታደርጉ ዘንድ መልዕክት እናስተላልፋለን።

@tikvahethiopia