TIKVAH-ETHIOPIA
'የንፁሃን ዜጎቻችን ስደት' ዛሬ ድረስ ባለው ሪፖርት መሰረት በትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን ውጊያ ሸሽተው ወደ ሱዳን የገቡ ሰዎች ከ25,000 አልፈዋል። UNHCR እና አጋሮቹ እገዛ ለማድረግ እየሰሩ የሚገኝ ሲሆን "ሃምዳያት" አካባቢ ያሉ የሱዳን ማህበረሰቦችም ምግብ እና የሚጠጣ እያቀረቡ ነው። * እየተደረገ ያለው እገዛ ግን አሁንም በቂ አያደለም ፤ ያለው ሁኔታ እጅግ በጣም አሳዛኝ ነው። @tikvahethiopia…
#UPDATE

ትግራይ ክልል እየተካሄደ ያለውን ውጊያ ሸሽተው ወደ ሱዳን የገቡ ሰዎች ከ30,000 ማለፋቸውን UNHCR ዛሬ ለቢቢሲ አሳውቋል።

ከቀን ወደ ቀን ቁጥሩ እየጨመረ መሄዱንም ገልጿል።

የUNHCR ድንገተኛ ምላሽ አስተባባሪ ጀንስ የሆኑት ሄዝማን በአካባቢው የሰብዓዊ ቀውስ መባባሱን ገልፀው ፤ ሁኔታው "አስጊ ነው" ብለውታል።

በድንጋጤ የተዋጡ እና እራፊ ጨርቅ ብቻ ላያቸው ላይ ጣል ያደረጉና በፍርሃት የተሞሉ ተፈናቃዮች ወደ ሱዳን ያቀኑ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ግማሽ የሚሆኑት ታዳጊዎች ናቸው።

UNHCR እንደገለፀው ትላንት ብቻ 2300 አዲስ ተፈናቃዮች ሱዳን ገብተዋል ፤ ከትናንት በስቲያ ደግሞ ከ5000 በላይ አዲስ ተፈናቃዮች ሱዳን መግባታቸውን ለቢቢሲ አሳውቋል።

@TIKVAHETHIOPIA @TIKVAHETHIOPIABOT