የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን...

#AddisAbeba

የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን በበአላት መዳረሻ ወቅት የሚፈፀሙ ወንጀሎችንና ህገ - ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ባከናወነው ኦፕሬሽን ህገ- ወጥ የጦር መሣሪያዎችን እና ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ጨምሮ በርካታ የወንጀል ፍሬዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል፦

- 11 ሽጉጦች ከ1600 በላይ መሰል የሽጉጥ ጥይቶች እንዲሁም ሀሰተኛ የብር ኖቶች ከማተሚያ ማሽን ጋር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

- ቅዳሜ ታህሣስ 25/2012 ዓ.ም ከጧቱ 2፡30 አካባቢ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው ኒያላ ሞተርስ ጀርባ ወንጀል የፈፀሙ 6 አባላት ያሉት አንድ የዘረፋ ቡድን በህብረተሰቡ ትብብር በሰዓታት ልዩነት ተጠርጣሪዎቹን ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

- በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ መርካቶ ሸክላ ተራ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከበርበሬ ጋር ባዕድ ነገር ቀላቅለው ለመሸጥ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 6 ተጠርጣሪዎች ከነ-ኤግዚቢቱ ሊያዙ ይችለዋል።

- ከተለያዩ ተሽከርካሪዎች ላይ 8 ተጠርጣሪዎች ከሰረቁት 331 ስፖኪዮ፤ የዝናብ መጥረጊያ እና ሌሎች የተሽከርካሪ አካላት፣ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ፣ላፕቶፕ ኮምፒውተር ፣ ቴሌቪዥን ፣ የቤት እና የግንባታ ዕቃዎች እንዲሁም ግራሙ ያልታወቀ አደዛዠ እፅ በተደረገ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ውሏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia