በየቤታችን እንወያይ!

የዚህች ሀገር ችግር ተመዞ አያልቅም። ከእናተው ጋር ሆኜ ብዙ እየሰማው እና እያየሁ እንደመዋሌ ላለፉት 3 ዓመታትም በየቀኑ እዚሁ ከናተው ጋር መረጃዎችን ስቀባበል ስውል እንደተረዳሁት ትልቁ ችግራችን ስለሰው ክቡርነት በሀገራችን ብዙ ስራ አልተሰራም። ዛሬ ዝርፊያው፣ ማሳደዱ፣ መግደሉ፤ ማፈናቀሉ...የምንሰማቸው ዘግናኝ ኢ ሰብዓዊ ወንጀሎች ሁሉ ሰው ምን ምንድነው የሚለውን በጥልቀት ካለመረዳት የመጣ ይመስለኛል። አንድን ሰው በሰውነቱ ካከበርነው ብሄሩን፣ ዘሩን፣ ቋንቋን፣ ማንነቱን...ሁሉንም እናከብርለታለን።

#በጥቅም ተደልለንም፤ በግለሰቦች ቅስቀሳም ወገናችንን የምንጎዳውም፤ ሰው የምናፈናቅለውም፤ ሰው የምንጠላውም #ሰውነትን በአግባቡ ስላልተረዳን ነው። መጀመሪያ ሰው እንሁን! ሰው ስንሆን የሌላው ሞት የኛ፤ የሌላው ስቃይ የኛ፤ የሌላው በደል የኛ ...ይሆናል! ሰውን ሁሉ እንደራሳችን ማየት ስንጀምር #ሰላም እንሆናለን።

ስለአንድነት፣ ስለነፃነት ፣ስለዴሞክራሲ ለማውራት በቅድሚያ እውነት እኛ #ሰውነት_ገብቶናል?? ብለን ልንጠይቅ ይገባል። ሁላችንም በሰውነት ጥላ ስር ከተከለልን የስቃይ እና የመከራ ጊዜው ያጥራል።

•እንደመነሻ ሀሳቤን ገልጫለሁ እናተስ ምን ትላላችሁ...?

ሀሳባችሁ ገፁ ላይ እንዲለጠፍ...👇

•በአማርኛ ፅሁፍ አጠር አድርጋችሁ ሀሳባችሁን ማቅረብ ወይም

•በድምፅ ከ4 ደቂቃ ያልበለጠ በጨዋ ቋንቋ የግል ምልከታችሁን ብቻ በ @tsegabwolde መላክ ይቻላል!

🔹ሚቀድመውን እናስቀድም! ከምንም ነገር በፊት ሰውነት ይቀድማል!! እውነት እኛ የሌላውን ስቃይ እንደራሳችን እናያለን?? ወይስ እኛን ሊያስለቅሰን የኛ ዘመድ ወይም የኛ ብሄር ሰው መሆን አለበት??
@tsegabwolde @tikvahethiopia