አስቸኳይ ጉባኤ‼️

የጋምቤላ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት 4ኛ የሥራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በመጪው #ቅዳሜ እንደሚካሄድ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስታወቁ።

አፈ ጉባኤው አቶ #ላክደር_ላክባክ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት አስቸኳይ ጉባኤው የሚካሄደው የክልሉን መንግስት የሚመራው ጋህዴን በቅርቡ ባካሄደው ግምገማ የክልሉ ዋናና ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ስልጣናቸውን ለመልቀቅ ያቀረቡትን ጥያቄ መሰረት በማድረግ ነው።

ለአንድ ቀን በሚካሄደው ጉባኤ የክልሉ ዋናና ምክትል ርዕሳነ መስተዳድሮች ያቀረቡት የስልጣን መልቀቅ ጥያቄ ለምክር ቤቱ ቀርቦ ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አፈ ጉባኤው ገልጸዋል።

በምትካቸውም አዲስ ዋናና ምክትል ርዕሳነ መስተዳድሮች እንደሚሾሙ ይጠበቃል ።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia