#update አምባሳደር #ሳህለወርቅ_ዘውዴ በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጣቸው የአሜሪካ ኢምባሲ የደስታ መግለጫ አስተላለፈ፡፡ ያለ #ሴቶች ተሳትፎ አንድ ማህበረሰብ #ውጤታማ እንደማይሆን የተገነዘበው የኢትዮጵያ መንግስት ሴቶችን ወደ ሃላፊነት ማምጣቱ ሊያስመሰግነው ይገባል ብሏል የአሜሪካ ኢምባሲ በመግለጫው፡፡ መንግስት ሴቶችን ያቀፈ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ጠንካራ እርምጃ በመውሰዱ ኢምባሲው #አድናቆቱን ገልጿል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia