TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BREAKING

በዛሬው እለት ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓ/ም ሜጀር ጀነራል አለምእሸት ደግፌ ወደ ሀገር መከላከያ ሠራዊቱ እንዲመለሱ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ ቀርቦላቸዋል - #PMOEthiopia

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#PMOEthiopia

ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት እውቅና ያላቸው ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጨምሮ ሁሉም ግለሰብ በወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ በመሬት ላይ ያለውን እውነታ የማያንፀባርቅ እና ያልተረጋገጠ መረጃ ከማሰራጨት እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#PMOEthiopia

የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል እያካደ የሚገኘውን "ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ" በብሔር ወይም በሌላ ወገንተኝነት ላይ የተቃኘ ነው የሚለውን የተሳሳተ እሳቤ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ዛሬ ህዳር 9/2013 ዓ/ም ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

እየተካሄደ ባለው "የህግ ማስከበር ዘመቻ" የትግራይ ህዝብ የመጀመሪያው ተጠቃሚ ይሆናል ሲል በመግለጫው ላይ ገልጿል።

* የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ያወጣው መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#DrAbdallaHamdok 

ዛሬ ጥዋት የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብደላ ሃምኮድ ለ2 ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ለሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የሱዳን የደህንነትና የፀጥታ እንዲሁም ወታደራዊ ባለስልጣናት አብረዋቸው መጥተዋል።

#PMOEthiopia
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#PMOEthiopia

በኢትዮጵያ ገለልተኛ የብሔራዊ ኢኮኖሚ ም/ቤት ተመሰረተ።

* ዝርዝር መረጃ እና የምክር ቤቱ አባላት ስም ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

@TIKVAHETHIOPIA
ከመጋቢት 27 ቀን 2013 ዓ.መ ጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተሰጡ ሹመቶች :

- መሐመድ ኢድሪስ መሐመድ የኢትዮጲያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

- ዮናታን ተስፋዬ ረጋሳ የኢትዮጲያ ብሮድካስት ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር

- ግዛው ተስፋዬ የኢትዮጲያ ብሮድካስት ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
'ምርጫው መራዘሙ አላስደሰተንም' - ክልሎች

ከጥር 2013 ዓ.ም. አንስቶ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ጋር በመሆን የክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች ለምርጫ የሚያደርጉትን ቅድመ ዝግጁነት ለመገምገም እና ለሚነሱ ጉዳዮች መፍትሄ ለመስጠት ስብሰባዎችን ሲያካሂዱ የጠ/ሚ ፅ/ቤት አስታውሷል።

ከእነዚህ ስብሰባዎች የቀጠለ ስብሰባ ዛሬ ተካሂዷል።

የዛሬው ስብሰባ ከምርጫ ቁሳቁስ አቅርቦት፣ የምርጫ ጣቢያዎችን ከማዘጋጀት፣ ከመራጮች ምዝገባ እንዲሁም ሰላማዊ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ምርጫ እንዲከናወን የጸጥታ አካላት ካላቸው ዝግጁነት አንጻር በየክልሉ ያለውን የቅድመ ዝግጁነት ስራ ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።

ከየክልሉ የተገኘው ሪፖርት ፥ በአጠቃላዩ የመራጮች ምዝገባ ቁጥር እና የምርጫ ፖሊሶችን አሰልጥኖ ዝግጁ የማድረግ ሂደቱ ጭማሪን ማሳየቱ ተመላክቷል።

የምርጫ ቦርድ መጪውን ምርጫ ለአጭር ጊዜ ማዘግየቱን አስመልክቶ፣ የክልል አመራሮች ምርጫው በቀደመው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እንዲካሄድ ለማስቻል ያላቸውን ዝግጁነት እና ቁርጠኝነት በመጥቀስ መራዘሙ 'አላስደሰተንም' ስለማለታቸው ተገልጿል።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት የሚኒስትሮች ምክር ቤት 100ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 100ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳለፈባቸው ጉዳዮች ፦

1.የፌዴራል የገቢ ግብር ደንብ፤
2. የመንግሥት ሠራተኞች እና የግሉ ዘርፍ ሠራተኞች ጡረታ ለመደንገግ በቀረቡት ረቂቅ ዐዋጆች ላይ ፤
3. የማዕድን ስምምነቶች
4. የተሐድሶ ሕክምና አገልግሎት ለማቋቋም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ ነው።

* ዝርዝር ጉዳዩ ከላይ ተያይዟል።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
ሹመት !

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በዛሬው ዕለት አቶ አብርሃም አለኸኝን በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዘርፍ አስተባባሪ አድርገው ሾመዋቸዋል።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
#NewsAlert

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 2ኛ መደበኛ ስብሰባው በኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

መንግስት በ6ኛው አገራዊ ምርጫ ይሁኝታ አግኝቶ ሲመረጥ ቃል ከገባባቸው አገራዊ ጉዳዮች መካከል ሁሉን አካታች የሆነ አገራዊ ምክክርና ውይይት በማካሄድ አገራዊ መግባባት እና በአገር ጉዳይ የጋራ አቋም እንዲኖር የሚያስችሉ ስራዎችን መስራት አንዱ መሆኑ ይታወቃል።

በዚሁ መሰረት መሠረታዊ በሚባሉ አገራዊ ጉዳዮች በተለያየ ጎራ የተሰለፉ የፖለቲካ ልሂቃንም ሆኑ ምልዓተ ህዝቡ ተቀራራቢና በአገራዊ አንድነት ገንቢ አቋም እንዲይዙ ለማድረግ አካታች አገራዊ ምክክሩን ተግባራዊ ለማድረግ በገለልተኝነት ለመምራትና ለማስተባበር የሚችል ቅቡልነት ያለው ተቋም ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ለውሳኔ ቀርቧል።

ምክር ቤቱም በቀረበው የማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ በዝርዝር ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ይጸድቅ ዘንድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
#Update

ወደር የሌለው የጥቁር አንበሳ ጀግና ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተሽለሙ ፦

1. ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ
2. ጀነራል አበባው ታደሰ
3. ጀነራል ባጫ ደበሌ
4. ሌ/ጀ አለምሸት ደግፌ

የአደዋ ድል ጀግና ከፍተኛ ሜዳይ በጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተሽለሙ ፦

1. ጀነራል ጌታቸው ጉዲና
2. ሌ/ጀነራል በላይ ስዩም
3. ሌ/ጀነራል ዘውዱ በላይ
4. ሌ/ጀነራል መሰለ መሠረት
5. ሌ/ጀነራል ሹማ አብደታ
6. ሌ/ጀነራል አብዱራህማን እስማኤል
7. ሌ/ጀነራል ይልማ መርዳሳ
8. ሌ/ጀነራል ሰለሞን ኢተፋ

የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት የመዘከሪያና የመከላከያ ሠራዊት ዋና መሥሪያ ቤት የማስመረቅ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

#PMOEthiopia #FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
#PMOEthiopia

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 5ኛ መደበኛ ስብሰባው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

(ዝርዝሩን ከላይ ያንብቡ)

@tikvahethiopia
#NewsAlert

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት የተለያዩ ሹመቶች ሰጥተዋል።

በዚሁ መሰረት፥

1. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር

2. አቶ ካሊድ አብዱራህማን - በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የፕሮጀክቶች ክትትል

3. አቶ ወንድሙ ሴታ - የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

4. አቶ ሄኖስ ወርቁ - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።

በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚከተሉትን ሸመቶች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲያጸድቅላቸው ጠይቀዋል፦

1. ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ዋና ኦዲተር

2. አቶ አበራ ታደሰ - የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ምክትል ዋና ኦዲተር

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#DrAbiyAhmed

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከህ/ተ/ም/ቤት አባላት እየተነሳላቸው ላለው ጥያቄ ማብራሪያ እና ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ።

በአሁን ሰዓት በፀጥታ እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ እና ምላሽ እየሰጡ ነው። በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በቀጥታ መከታተል ይቻላል።

ዋና ዋና ነጥቦችን ተከታትለን እናሳውቃለን።

እስካሁን ድረስ ያነሷቸው ጉዳዮች እና ተጠይቀው ማብራሪያ የሰጡባቸው (ከፀጥታ ጉዳዮች ውጭ) በዚህ ተያይዟል : https://telegra.ph/PM-Abiy-Ahmed-06-14

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DrAbiyAhmed ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከህ/ተ/ም/ቤት አባላት እየተነሳላቸው ላለው ጥያቄ ማብራሪያ እና ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ። በአሁን ሰዓት በፀጥታ እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ እና ምላሽ እየሰጡ ነው። በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በቀጥታ መከታተል ይቻላል። ዋና ዋና ነጥቦችን ተከታትለን እናሳውቃለን። እስካሁን ድረስ ያነሷቸው ጉዳዮች እና ተጠይቀው ማብራሪያ የሰጡባቸው (ከፀጥታ ጉዳዮች…
#ድርድር

ካለፉት ሳምንታት ጀምሮ መንግስት ከTPLF ጋር ድርድር ሊያደርግ እንደሆነ የተለያዩ ምንጫቸው በግልፅ ያልተገለፁ/ ያልተረጋገጡ መረጃዎች ሲወጡ ነበር።

ዛሬ ከህ/ተ/ም/ቤት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ድርድርን በተመለከተ መረጃ ሰጥተዋል።

" ከማንም ጋር ሰላም ነው የምንፈልገው። " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ፤ " እያንዳንዷ የሰላም ቀን ለእኛ ትርፍ ታስገኝልናለች። ሕዝብ ሳያውቀው የሚደረግ ድርድር የለም። " ብለዋል።

አክለውም ፥ " በይፋ የታወቀ አጥኚ ኮሚቴ ተቋቁሞ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካኝነት እየተመራ ሲሆን፣ እስካሁን ውጤቱን አላሳወቀም። የሚደራደረው ኮሚቴም ይሄ ነው። " ብለዋል።

" ውጊያ ሲመጣ ለሕዝብ አሳውቀን የጀመርን ሰዎች፣ ድርድር ከተጀመረ የሚያስደብቀን ነገር የለም። ነገር ግን፣ የብቻ ጠላት የለም የሀገር ጠላት እንጂ፣ ለብቻም የሚሰራ ሥራ የለም በጋራ እንጂ። " ሲሉ ለምክር ቤቱ ተናግረዋል።

የእኛም የሕዝባችንም ፍላጎት ለጥይት የሚወጣ ውጪ ለልማት እንዲወጣ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ሰላም እንፈልጋለን ማለታችን የተደበቀ ድርድር እናደርጋለን ማለት አይደለም " ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ፦
- በፀጥታ ተቋማት ዝግጅት፣
- በህግ ማስከበር፣
- በ ' ተረኝነት ' ጉዳይ ፣
- በማህበራዊ ሚዲያዎች ጉዳይ ፣
- ሌብነትን በተመለከተ፣
- የብሄራዊ ምክክሩን በተመለከተ የሰጧቸው ምላሽ እና ማብራሪያዎች በዚህ ታገኛላችሁ https://telegra.ph/PM-Abiy-Ahmed-06-14-2 (#PMOEthiopia)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሚኒስትሮቹ ወዴት ነው የተሸኙት ? ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ፦ - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞግስ፤ - የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ፤ - የግብርና ሚኒስትር አቶ ኡመር ሁሴን፤ - የጠ/ሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ተፈሪ ፍቅሬን ዛሬ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት መሸኛታቸውን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።…
#ሹመት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ለከፍተኛ የመንግስት ኃላፊነት ቦታዎች ሹመቶች በመስጠት የህ/ተ/ም/ቤት ሹመቱን እንዲያፀድቅላቸው ጠይቀዋል።

በዚህም መሰረት፦

1.  ዶክተር ዓለሙ ስሜ - የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር፣

2.  ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ - የማዕድን ሚኒስትር፣

3.  ዶክተር ግርማ አመንቴ - የግብርና ሚኒስትር

እንዲሁም ከጥር 10 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ፦

1.  አቶ ማሞ ምሕረቱ - የብሔራዊ ባንክ ገዢ፣

2.  ወይዘሮ አለምፀሐይ ጳውሎስ - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር፣

3. ዲያቆን ዳንኤል ክብረት - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር፣

4.  አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ፖሊሲ አማካሪ ሚኒስትር እና

5.  አቶ መለሰ አለሙ - በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት  ግንባታ ማስተባበሪያ የዘርፍ አስተባባሪ ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ተሹመዋል፡፡

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
#PMOEthiopia

ዛሬ ማክሰኞ የሚኒስትሮች ምክር ቤት 18ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዶ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።

ም/ቤቱ ከተወያየባቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ማቋቋሚያ ደንብ ለማሻሻል በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የተፈቀደ እና የተከፈለ ካፒታል በማሻሻል የተቋቋመበትን ዓላማና ተልዕኮ ለማሳካት እንዲችል በተለይ ፦

- በግንባታ ላይ ያሉ የባቡር መሰረተ ልማቶች እንዲጠናቀቁ የተጠናቀቁትም ወደ ስራ እንዲገቡ፤

- በቀጣይ ለሚገነቡ የባቡር መሠረተ- ልማቶች የተሻለ አቅም እንዲኖረው የተፈቀደ ካፒታሉ ወደ ብር 221 ቢሊዮን ከፍ እንዲል በጥሬ ገንዘብና በአይነት የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ ብር 120 ቢሊዮን እንዲሆን ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ መቅረቡ ተገልጿል።

ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ ተወያይቶ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

(ተጨማሪ የዛሬ የምክር ቤቱን ወሳኔዎች ከላይ ያገኛሉ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ? " አጠቃላይ የሀገራችን የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታዎች በዋና ዋና አመላካቾች በምን ደረጃ  ላይ ናቸው ? በተለይ የኑሮ ውድነት እየከፋ ነው። የዋጋ ንረትን ደግሞ ማረጋጋት አልተቻለም። በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለው ማህበረሰብ እና የመንግሥት ሰራተኛው መኖር አቅቶታል። መኖር የቅድሚያ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው። ስለሆነም እንደ መንግሥት በቀጣይ አመታት…
#DrAbiyAhmed

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የኑሮ ውድነትን በተመለከተ ለተጠየቀው ጥያቄ ምን መለሱ ?

" የኑሮ ውድነት የበርካታ ሀገራት ፈተና ሆኖ ቀጥሏል፡፡

በአንዳንድ ሀገራት ከ60 በመቶ በላይ የደረሰ የዋጋ ንረት እየተመዘገበ ነው፡፡

በኢትዮጵያም የኑሮ ውድነት ጫናን ለመቀነስ መንግስት በርካታ ኢንሸቲቮችን ቀርጾ እየሰራ ነው፡፡

በተለይ የሌማት ትሩፋት የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት ከፍተኛ ሚና እያበረከተ ይገኛል፡፡

ምርታማነትን ማሻሻልም ሌላኛው ስራ ነው፡፡

በዘንድሮው ዓመት ከዓለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ከ100 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ብልጫ ያለው ምርት መሰብሰብ ተችሏል፡፡

በተጨማሪም መንግስት 10 ቢሊዮን ብር ገቢ በመተው መሰረታዊ ሸቀጦችን ከቀረጥ ነጻ እንዲገባ አድርጓል፡፡

ይህ ሁሉ የሚከናወነው የኑሮ ውድነቱ ዜጎቻችን ላይ የሚያደርሰውን ጫና ለማቃለል ነው፡፡ በዚህም የዋጋ ንረቱን ባለፈው ዓመት ከነበረበት 30 በመቶ ወደ 23 በመቶ ዝቀ ማድረግ ተችሏል፡፡ "

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ስብሰባውን አድርጎ ዓለም ዐቀፍ የልማት ማህበር ጋር የተደረገውን የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት በማጽደቅ ለሕ/ተ/ም/ቤት እንዲላክ ወስኗል።

ምክር ቤቱ ምን አለ  ?

- የተደረገው የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት የ1.5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚያስገኝ ነው። ከዚህ ውስጥ 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በእርዳታ፣ 500 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደግሞ በብድር መልክ የተገኘ ነው፡፡

- የፋይናንስ ድጋፉ ፦
° የኢትዮጵያ መንግሥት የማክሮ ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት የጀመራቸውን የሪፎርም ሥራዎች ለማስፈጸም
° ለሥራ ፈጠራ፣
° የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር፣
° የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመቅረፍ፣
° የመዋቅር ማስተካከያ ለማድረግ እንዲሁም የፌደራል መንግሥት የ2ዐ17 ዓ.ም በጀትን በቀጥታ ለመደገፍ የሚውል ነው፡፡

- ብድሩ ከወለድ ነፃ ፣ የ6 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ38 ዓመታት ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው። ከአገራችን የብድር አስተዳደር ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣምም ነው።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia