TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#HARGEISA

በሶማሊላንድ ሁለተኛ (2) ሰው በኮቪድ-19 መሞቱ ሪፖርት ተደረገ ፤ በዛሬው ዕለት ህይወታቸው እንዳለፈ የተገለፀው ግለሰብ የሀርጌሳ ነዋሪ ሲሆኑ ምንም አይነት የጉዞ ታሪክ እንደሌላቸው ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#Hargeisa

የሶማሊ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ሶማሌለንድ፣ ሃርጌሳ ይገኛሉ።

የክልሉ ፕሬዜዳንት በእሳቸው የሚመራ ከፍተኛ የመንግሥት ልዑካን ቡድንን ይዘው ነው ዛሬ ከሰዓት ሀርጌሳ የገቡት።

ወደሶማሌላንድ ያቀናው ልዑክ ፦ የሶማሊ ክልል ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙባሽር ዲባድ ራጌ፣ የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲራህማን ኢድ ጣሂርና ሌሎች የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራር አካላት የሚገኙበት ነው።

ልዑካን ቡድኑ ከሶማሌላንድ መንግሥት ጋር በጸጥታ፣ በንግድ ትስስርና በሌሎች የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከክልሉ ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia