TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Malawi

ዛሬ የማላዊውን ምክትል ፕሬዝዳንት ሳውለስ ቺሊማን እና ሌሎች 9 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን ተሰውሯል።

እንደ አገሪቱ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት መረጃ አውሮፕላኑ የማላዊ መከላከያ ኃይል ንብረት ነው።

ጥዋት ከሀገሪቱ ዋናው ከተማ ሊሎንዌ ከተነሳ በኋላ " ከራዳር ዕይታ ውጪ " ሆኗል። ምን ውስጥ ይግባ አይታወቅም።

የአገሪቱ የአቪዬሽን ባለሥልጣናት ከአውሮፕላኑ ጋር ግንኙነት ለማድረግ ሞክረው ነበር ግን አልቻሉም።

የሀገሪቱ ፕሬዝዳንትም #የፍለጋ እና #ነፍስ_የማዳን ተልዕኮ እንዲካሄድ አዘዋል።

ም/ ፕሬዝዳንቱ መንግሥትን ወክለው በአንድ የቀድሞ የም/ቤት አባል የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ነበር በረራ የጀመሩት።

አብረዋቸው በርካታ የፓርቲያቸው ባለሥልጣናት ነበሩ።

Credit : #BBC

@tikvahethiopia