TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ፌደራል ፖሊስ⬆️

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የሰው ሀይሉን ለማጠናከር ለ16ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን ከ5ሺህ በላይ ምልምል ፖሊሶችን በዛሬው እለት አስመርቋል፡፡ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሞሽነር ጀነራል ይደህጎ ስዩም ለተመራቂዎች መመረቃቸውን በማብሰር ወደተመደቡበት የስራ ቦታ ሲሄዱ ሀገራቸው የጣለችባቸውን አደራ በብቃት እንዲወጡ እና #የህግ_የበላይነት እንዲሰፍን ጠንክረው እንዲሰሩ ከአደራ ጭምር የስራ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የመደበኛና ልዩ ልዩ ሙያ ስልጠና ዳይሬክተር ኮማንደር ተስፋዬ ወንድሙ እነደገለጹት ምልምል ፖሊሶች ከመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ወጣቶች መሀከል መስፈርቱን በማሟላት የተመለመሉ መሆናቸውን በማስታወስ ለተከታታይ 8 ወራት በፖለስ ሙያ የተለያዩ ስልጠናዎችን በብቃት የተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የስልጠና ሀላፊው እነደገለጹት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶቸች በተገኙበት በጦላይ ማሰልጠኛ መዕከል ስነስረአቱ ተከናወናል ብለዋል፡፡ ፖሊስ መኮነኑ አየይዘውም ከተመረቂዎች መሀከል 822 ምልምል የሴት ፖሊሶች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፦ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#udate ሳምንታዊ የመንግስት መግለጫ⬇️

በኢትዮጵያ #የህግ የበላይነትን ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ አስታወቀ።

የአገሪቷን ሰላም፣ ልማት እና ዴሞክራሲ ለማረጋገጥ የህግ የበላይነት መከበር እንዳለበት የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በላከው ሳምንታዊ የመንግስት አቋም መግለጫው አመልክቷል።

በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ለውጥ ለህዝቦቿ ተስፋ ሰጪ ከመሆኑ በላይ ከአገር አልፎ ለአጎራባች የአፍሪካ አገሮች ጭምር ተምሳሌት መሆኑን የታወቁ የዓለም ፖለቲካ ተንታኞችና ተቋማት እየመሰከሩለት መሆኑን ጠቅሷል።

ይሁን እንጂ ለውጡን የማይደግፉ ቡድኖች አንዳንድ አደናቃፊ ተግባራትን ሲፈፅሙ እንደሚስተዋል አመልክቷል።

እነዚህ አካላት ከሰሞኑ በቡራዩ እና በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ባስነሱት ግጭት የሰው ህይወት ጠፍቷል፤ “የዜጎች ጥሪትም ወድሟል” ሲል አመልክቷል።

“የንፁሃን ዜጎችን ደም ማፍሰስ፣ አካል ማጉደል እና ለዓመታት ለፍተውና ደክመው ያፈሩትን ሃብት በመዝረፍና በማውደም፤ ሁሉም የሚረባረብለትን የለውጥ ጉዞ ለማጠልሸት መስራት ለማንም ትርፍ አያስገኝም” በማለትም አስገንዝቧል።

በመሆኑም በደረሰው ጉዳት ህዝብ እና መንግስት አዝነዋል ያለው የመንግስት መግለጫ “ድርጊቱ የየትኛውንም ብሄር የማይወክል እና ክስተቱ ለውጡን የሚያፋጥን እንጂ ሊያደበዝዝ አይችልም” ብሏል።

በአዲሲቷ ኢትዮጵያ ከእንግዲህ ማሸነፍና ሥልጣን መያዝ የሚቻለው የተሻለ ሃሳብ በማቅረብ ተወዳድሮ በማሸነፍ እንጂ #በአመጽና በኃይል ሊሆን እንደማይችልም በመግለጫው ተመልክቷል።

የህግ የበላይነት ባልሰፈነበት ሁኔታ የአገሪቷን #ሰላም፣ ልማት እና ዴሞክራሲ ማረጋገጥ የማይቻል በመሆኑ መንግስት ኃላፊነቱን ለመወጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ ለህግ የበላይነት #መከበር በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቤንሻንጉል ክልል⬇️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኦዳ ዳለቲ እና በጉባ አልመሃል ላይ በተፈጠሩ ግጭቶች 69 ተጠርጣሪዎችን #በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የክልሉ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ፡፡

የክልሉ መንግስት #የህግ የበላይነትን ለማስከበር ከፌደራልና ከአጎራባች ክልሎች ጋር እየሰራ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

የከልሉ መንግስት የህግ የበላይነት ለማስከበር #ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር እያዋለ ይገኛልም ብለዋል፡፡

ነሐሴ 26 እና 27 2010 ዓ'ም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኦዳ ቢልዲጊሉ ወረዳ ዳለቲ ቀበሌ ላይ በተፈጠረው ግጭት 48 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዉለዉ የማጣራት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡

ግጭቱ በቤኒሻንጉልና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ አከባቢ ላይ የተከሰተ በመሆኑ የማረጋጋት ስራዉንም ሆነ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር
የማዋል ሂደቱ በጋራ እየተሰራ እንደሚገኝ ነዉ አቶ ማሃመድ የተናገሩት፡፡

በተመሳሳይም መስከረም 3 2011 ዓ.ም በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ አልመሃል ቀበሌ ላይ በደረሰዉ ጥቃት 21 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተካሄደባቸዉ ይገኛል፡፡

ሰኔ 17 እስከ 21 በአሶሳ ከተማ፣ በሽርቆሌ ወረዳ እና በማኦኮሞ ልዩ ወረዳ ላይ ተከስቶ በነበረዉ ግጭት በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸዉ በፍርድ ቤት እየታየ መሆኑንም አቶ መሃመድ ገልፀዋል፡፡

#በአሶሳ ከተማ እና በሸርቆሌ ወረዳ ላይ ተከስቶ በነበረዉ ግጭት ከ 1 መቶ በላይ የሚሆኑ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል የኦፕሬሽ ስራ እየተሰራ ነዉ ብለዋል፡፡

የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር ጥረት እያደረገ ነዉ ያሉት ሃላፊዉ ከፌደራል መንግስት የተላከ ቡድን እንዳለም ተናግረዋል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወንጀልን በጋራ እንከላከል‼️

የዜጎች ነፃነት ሳይሸራረፍ ይከበር ዘንድ #የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ ግድ ይላል። ወንጀልን መርምሮ ወንጀለኛን ከማስቀጣት ደግሞ ወንጀልን ቀድሞ መከላከል ይሻላል።

ማንኛዉም ዜጋ በሚከተሉት ቁጥሮች ጥቆማ መስጠት ይችላል!

የፌዴራል ፖሊስ፦
0115543678/
0115526303/
0115543681/
987

አዲስ አበባ ፖሊስ
0111110111/
991

ኦሮሚያ ፖሊስ፦
0118722020/
0113692452

አማራ ፖሊስ፦
0582201327

ደቡብ ፖሊስ፦
+251462212870

እነዝህ ስልኮች 24 ሰዓት ክፍት ናቸዉ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሀረሪ ክልል⬇️

የሕግ የበላይነትን ለማስከበር እና ህገ ወጥነትን ለማስቀረት የሚሰራ ኮሚቴ ማቋቋሙን የሐረሪ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሙራድ አብዱልሀዲ ገልፀዋል፡፡

የሐረሪ ክልል ርዕስ መስተዳር አቶ ሙራድ አብዱልሀዲ አገራችን በለውጥ ውስጥ እንዳለች ትላንት በሰጡት መግለጫ አስረድተዋል፡፡

ይሁን እንጂ ለውጡን የማይፈልጉ ጥቅማቸው የተነካ አካላት በእምነትና በጎሳ #ግጭት ለመፍጠር እየጣሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በክልላችንም አልፎ አልፎ ይኸው ሁኔታ እንደሚስተዋል ገልፀዋል ፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ በመቀጠልም #የህግ የበላይነትን ለማስከበር በክልሉ ምክር ቤት የሰላም ኮሚቴ መቋቋሙን ገልጸዋል፡፡

በከተማዋ የተከማቸውን #ቆሻሻ አስመልክቶም የከተማዋ ነዋሪዎች እስካሁን ላሳዩት #ትእግስት ምስጋና አቅርበው ቆሻሻው በቀጣዮቹ ሁለት
ቀናት ውስጥ ይወገዳል ብለዋል፡፡

በፀጥታው በኩል #ከቄሮ እና #ፋኖ ጋር አብሮ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ባሉበት ቦታ #ሰኞ ምክክር እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፦ የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አድዋ🔝በአዳዋ እየተካሄደ በሚገኘው ሰልፍ ነዋሪዎች #የህግ የበላይነት #እንዲከበር በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጠ/ሚ ፅ/ቤት‼️

መንግስት #የህግ_የበላይነትን ለማረጋገጥ ቁርጠኛ አቋም መያዙን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት አስታወቀ፡፡

ሴክሬታሪያቱ ዛሬ በሰጠው ሳምንታዊ መግለጫ ላይ እናዳለው በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች ከህግ ያፈነገጡ ሁኔታዎች ይስተዋላሉ፡፡

መንግስት ይህን ሁኔታ ለማስቆም ቁርጠኛ አቋም ይዟል ብሏል ሴክሬታሪያቱ፡፡

የህግ የበላይነትን ለማረጋገጡ እየተወሰደ ያለው እርምጃ በአንድ ብሔር ላይ ያነጣጠረ ነው የሚለው አስተያየትም የተሳሳተ መሆኑን ነው ሴክሬታሪያቱ የገለፀው፡፡

በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄዱ ያሉት ሪፎርሞች ለአገራዊ ችግሮች አገር በቀል መፍትሔዎች የማበጀት ዓላማ ያላቸው መሆናቸውንም ጠቅሷል ሴክሬታሪያቱ፡፡

አገራዊ ለውጡ ከውስጥም ከውጭም ትልቅ እውቅና የተቸረው ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ ድጋፍም እያስገኘ ያለ ነው ብሏል፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ አስተማማኝ ሰላምን በማስፈን የሕዝብን #ደኅንነት ማስከበር የመንግሥት ቀዳሚ ተግባር ነው! #ሕገ_ወጦችና ወደሕግ የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!

🔹🔹ብሔራዊ የጸጥታ ምክር ቤት🔹🔹
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቡታጅራ🔝በጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ሰልፍ ተካሄደ። ሰልፈኞቹ መንግስት በመስቃንና ማረቆ ብሔረሰቦች መካከል የተፈጠረውን ችግር እንዲፈታ፣ #የህግ_የበላይነት እንዲያስከብርና ተፈናቃይ ዜጎችን እንዲደግፍ ጠይቀዋል።

©elu ©Bedilu
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ #የህግ_የበላይነትን በማስከበር የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እየመከረ መሆኑን የአራቱ ብሄራዊ ድርጅቶች ተወካዮች ተናግረዋል።

via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የሚፈፀሙ የጥላቻ ንግግሮችን #ለመቀነስ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ አስታወቁ፡፡ አጥፊዎችን #ተጠያቂ የሚያደርጉ #የህግ ማዕቀፎች ተግባራዊ ይደረጋሉም ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አልጀዚራ
@tsegabwolde @tikvahethiopi
ጌዴኦ‼️

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሬስ ሴክሬቴሪያት አቶ ነጉሱ ጥላሁን #በጌዴኦ ላሉ ተፈናቃዮች የዕለት ምግብ ተደራሽ ለማድረግ መንግሥት #ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። መንግሥት የዕለት ደራሽ ምግብ ለሚያስፈልጋቸው #ድጋፍ ለማድረግ ከፌደራል እና ከክልል ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ከዚህ ቀደምም ሲሰራ ቆይቷል፤ በዚህም እንዲቋቋሙ የተደረጉ እንዳሉም ገልጸዋል።

ነገር ግን አሁንም #የዕለት_ደራሽ_ምግብ ያልደረሳቸው ዜጎች እንዳሉ እና ችግር ላይ እንደወደቁ መንግሥት ተረድቶ የዕለት ምግብ ተደራሽ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶት ተጎጂዎችን በዘላቂነት ለማቋቋም እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል። ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ዜጎችን በማቋቋም፣ #የህግ_የበላይነትን በማረጋገጥ የሚደርሱ ማፈናቀሎችን ማስቆም መቻል ላይ መንግሥት ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የህግ_ጉዳይ

ከክልል ፍርድ ቤቶች እስከ ፌዴሬሽን ደርሶ ወደ ከፍተኛ የተመለሰው የንብረት ክርክር መጨረሻ ምን ይሆን ?

(በሪፖርተር ጋዜጣ - አሳዬ ቀፀላ)

ከ10 ዓመታት በፊት ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነበር ክርክሩ የተጀመረው።

የክርክሩ መነሻ፣ በኦሮሚያ ክልል በቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ጌትእሸት ዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ሽያጭ ነው፡፡

ድርጅቱ የእነ ጌታቸው እሸቱ (ኢንጂነር) አራት ሰዎች ሲሆን፣ ጠቅላላ የቦታው ስፋት 11,305 ካሬ ሜትር ነው፡፡

የዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ፋብሪካው ያረፈው በ3,015 ካሬ ሜትር ላይ ሲሆን፣ ስመ ሀብቱ የተመዘገበው በጌታቸው እሸቴ (ኢንጂነር) ስም ነው፡፡

ቀሪው 8,290 ካሬ ሜትር ደግሞ ጅምር ግንባታ ያለበት ሆኖ፣ ስመ ሀብቱ (ካርታው) የተመዘገበው በጌትእሸት ዲተርጀንት ማምረቻና ማሸጊያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስም ነው፡፡

ፋብሪካውንና ጅምር ግንባታ ያረፈበትን (በሁለት የተለያዩ ስሞች የተመዘገቡ ይዞታዎች) ሁለት ይዞታዎች እነ ጌታቸው (ኢንጂነር) (አራት ሰዎች) ለእነ ዶ/ር በዕውቀቱ ታደሰ ከአሥር ዓመታት በፊት ኅዳር 18 ቀን 2005 ዓ.ም. በ22,500,000 ብር ሸጠውላቸዋል፡፡

የሽያጭና የግዥ ውሎች የኢትዮጵያ ፍትሐ ብሔር ሕጎችን ሒደት በጠበቀ ሁኔታ ተፈጽመዋል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/Justice-08-06

@tikvahethiopia
#ETA

" ማንኛውም የግል ትምህርት ወይም ስልጠና ተቋም #የመምህርነት እና #የህግ ትምህርት ዘርፎችን ማስተማር አይችልም "

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ፤ ባዘጋጀው የከፍተኛ ትምህርትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ፈቃድ አሰጣጥ ረቂቅ መመሪያ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወይም የስልጠና ተቋማት በሁሉም መርሃ ግብሮች #የሕግ እና #የመምህርነት ትምህርት ዘርፎችን #አሁንም ማስተማር እንደማይችሉ ተገልጿል።

ከዚህ በፊትም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁሉም መርሃግብሮች የሕግ እንዲሁም የመምህርነት ትምህርት እንዳይሰጡ የተደረገ ሲሆን አሁንም በአዲሱ መመሪያ የሕግ እና የመምህርነት ትምህርት መስጠት አይችሉም ተብሏል።

ሌሎች በአዲሱ የከፍተኛ ትምህርትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ፈቃድ አሰጣጥ #ረቂቅ መመሪያ ላይ ምን ተካቷል ?

- ማንኛውም ተቋም አዲስ ፕሮግራም ለመከፈት ወይም ነባሩን ፕሮግራም ለማስቀጠል የፍላጎት ዳሰሳ፣ የገበያ ጥናት እና ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ እውደ ጥናት ማካሄድ ይኖርበታል፡፡

- ለማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት የፕሮግራም ፈቃድ የሚሰጠው ባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) የሚያወጣቸውን መስፈርቶች አሟልተው ሲገኙ ብቻ ይሆናል፡፡

- የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከፍቷቸው ፕሮግራሞች ባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) የሚያወጣቸውን የመመዘኛ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡

- ለማንኛውም ተቋም የሚሰጥ ፈቃድ የሚያገለግለው በባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) ተገምግሞ ለተፈቀደለት ካምፓስና የትምህርት መስክ ብቻ ይሆናል።

- ማንኛውም ተቋም የጤና የትምህርት መስኮችን መስጠት የሚችለው በመደበኛ መርሃ ግብር ብቻ ይሆናል፡፡

- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በርቀት ትምህርት መርሃ ግብር ማስተማር የሚችለው ከድንበር ተሻጋሪ ወጪ በመጀመሪያ ዲግሪ ብቻ ይሆናል።

- ማንኛውም የግል ትምህርት ወይም ስልጠና ተቋም #የመምህርነት እና #የህግ ትምህርት ዘርፎችን ማስተማር አይችልም፡፡

- ማንኛውም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋም የትኛውንም ስልጠና በርቀት መርሃ ግብር ለማሰልጠን የሚቀርብ የፈቃድ ጥያቄ የማይስተናግድ ይሆናል።

- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም #በህክምና_ዶክትሬት እና #በስፔሻሊቲ ትምህርት ፈቃድ ለማግኘት ተቋሙ #የህክምና_ሆስፒታል ሊኖረው ይገባል።

- በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተቋም ደረጃ የጸደቀ ስርዓተ ትምህርት የፈቃድ ጊዜው ሳያበቃ የስርዓተ ትምህርት ወይም የዲግሪ ስያሜ ለውጥ ካለባለስልጣኑ ፈቃድ ወጪ ማድረግ አይችልም።

- በሀገር ደረጃ በትምህርት ፖሊሲ ስርዓተ ትምህርቱ እስካልተቀየረ ድረስ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተቋም ወይም በካምፓስ ደረጃ የጸደቀ ስርዓተ ትምህርት የፈቃድ/ፈቃድ እድሳት ጊዜው እስካላበቃ ድረስ በሌሎች ካምፓሶች መተግበር ወይም መጠቀም ይችላል።

- የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በበየነ መረብ ወይም በርቀት ትምህርት መርሃ-ግብር ፈቃድ ሲጠይቁ በባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) ስርዓተ-ትምህርቱ ቀድሞ መገምገም እና ተገቢ ማስተካከያ ተደርጎ መፅደቅ ይኖርበታል።

- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በብሎክ ኮርስ ትምህርት ለመስጠት ያለው አመቺነትና ተገቢነት እንዲሁም የትምህርት ጥራት ላይ የሚኖረውን ተፅህኖ ከግምት በማስገባት ስርዓተ ትምህርቱ ከጸደቀ በኃላ ሊተገብር ይችላል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያገኘው ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን መሪ አስፈፃሚ ሕይወት አሰፋ ነው።

@tikvahethiopia
#አሁን #ሲዳማ

የሲዳማ ክልል ም/ ቤት አስቸኳይ ጉባዔ በሀዋሳ እያካሄደ ነው።

ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው እያካሄደ ያለው።

ለአንድ ቀን ብቻ ይካሄዳል በተባለው በዚህ አስቸኳይ ጉባኤ በሶሰት የተለያዩ አጃንዳዎች ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሏል።

- ለጉባኤው ሞሽን ቀርቦ ይጸድቃል።

- የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ የስራ ሃላፊዎች ሹመት ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀድቃሉ።

- የምክር ቤቱ አባላት #የህግ_ከለላ ማንሳት ላይ ተወያይተው ውሳኔ ይሰጣሉ።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF

ከወራት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የህወሓት (TPLF) ሊቀመንበር ዶክተር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የተሳተፉበት ውይይት ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድና ከሌሎች ከፍተኛ የፌዴራል ባለስልጣናት ጋር መደረጉ ይታወሳል።

በወቅቱም ከ ' ህወሓት ' ህጋዊ እውቅና  ማግኘት ጋር በተገናኘ ውይይት ተደርጎ ነበር።

አቶ ጌታቸው ረዳ ከውይይቱ በኃላ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫቸው ፤ ' ህወሓት / TPLF ' መልሶ እንደ ፓለቲካ ፓርቲ የመመዝገብ ጉዳይ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ የፌደራል መንግስት እንደማይደግፈው ገልጸው ነበር።

በዚህም ያለው #የህግ_ክፍተት በአስቸኳይ ታርሞ ምዝገባው እንዲፈፀም መመራቱን ሲናገሩ ተደምጠው ነበር።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም ሲል የ ' ህወሓት ' ን ህጋዊ ሰውነት #መሰረዙ ይታወቃል።

ፓርቲውም " ስረዛው ይነሣልኝ " ሲል ጥያቄ ቢያቀርም ቦርዱ ያን ሊያደርግ የሚችልበት ምንም ህጋዊ መንገድ እንደሌለ አሳውቆ ነበር።

ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያሳለፈው " የኢትዮጵያ የምርጫ ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ " ምናልባትም ህወሓት ዳግም እውቅና ሊያስገኝለት የሚያስችለው እንደሆነ እየተነገረ ነው።

@tikvahethiopia