TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
“ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” - ስፔንሰር ኮክስ

የአሜሪካ ሀገር " ዩታህ ግዛት " በታዳጊዎች ፌስቡክ፣ ቲክቶክ እና ኢነስታግራምን የመሰሉ ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸው ላይ ገደብ ጣለች።

ይህ በማድረግ አሜሪካ ውስጥ የመጀመሪያዋ ግዛት ሆናለች።

ትላንት ሀሙስ በፀደቀው ደንብ መሰረት ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም#ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።

የፀደቀው ደንብ ምን ይዟል ?

- የማኅበራዊ ሚዲያ አገልግሎት አቅራቢ ኩባንያዎች ለልጆች አገልግሎቱን ከማቅረባቸው በፊት #የወላጆችን ይሁንታ ማግኘት ይኖርባቸዋል።

- ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም#ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።

- ኩባንያዎች መተግበሪያዎቻቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ አዳጊዎች ያለ ወላጅ ይሁንታ እንዳይከፍቱ ያደረጋሉ።

- ኩባንያዎቹ የአዳጊዎቹን የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ታሪክ፣ የለጠፏቸውን እና በግል #የተጻጻፏቸውን_መልዕክቶች ሁሉ ለወላጆች መስጠት ይገደዳሉ።

- የማኅበራዊ ሚዲያ አቅራቢ ኩባንያዎች የልጆቹን ፍላጎት እና ምርጫ መሠረት አድርገው #ማስታወቂያ በልጆቹ የማኅበራዊ ሚዲያ ሰሌዳቸው ላይ እንዳይለቁ ይገደዳሉ።

- ታዳጊዎች ማኅበራዊ ትስስር መድረኮችን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ንጋት 12፡30 ድረስ መጠቀም እንዳይችሉ ይደነግጋል።

ሕጉ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ከሚቀጥለው ዓመት መጋቢት ጀምሮ ነው።

ይህን እርምጃ መውሰድ ያስፈለገው ማኅበራዊ የትስስር መድረኮች በልጆች #የአእምሮ_ጤና ላይ ከፍ ያለ መረበሽን እያደረሱ መሆኑ ከተደረሰበት በኋላ ነው ተብሏል።

የዩታህ ግዛት ገዢ ስፔንሰር ኮክስ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፤ “ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” ሲሉ ጽፈዋል።

ከዩታህ በተጨማሪ ተመሳሳይ ሕጎች በቴክሳስ፣ በኦሃዮ፣ በአርካንሳስ፣ በኒው ጀርሲ እና በሊዊዚያና ግዛቶች እየተረቀቁ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።

Credit : #BBC

@tikvahethiopia
#ADHD

የስዊድን መንግሥት ፦
° ጥንቃቄ የጎደለው ትኩረት የማጣት፣
° ከፍተኛ የመቅበጥበጥ፣ 
° ብዙ የማውራት፣
° ግትርነት
° እራስን የመግዛት ቀውስ (ADHD -attention deficit hyperactivity disorder) ችግር በብዛት የሚታይባቸው ልጆች በሀገሪቱ ቁጥራቸው መጨመሩን ዛሬ አስታወቀ።

የሀገሪቱ የማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ቃል የስዊድን የጤና እና ደህንነት ቦርድ መረጃ ADHD ተብሎ የሚገለጸው #የአእምሮ_ጤና_ችግር እ.ኤ.አ. ከ2022 ጀምሮ 10 በመቶ በሚሆኑ ወንዶች ልጆች ላይ እንዲሁም 6 በመቶ በሚሆኑት አዳጊ ሴት ልጆች ላይ በምርመራ መታየቱን ይፋ አድርጓል።

የችግሩ ተጋላጭ ልጆች ቁጥር ሊጨምርም ይችላል ተብሏል።

በመላው ዓለምም ከ5 እስከ 7 በመቶ የሚሆኑ ልጆች ለዚህ ችግር የተጋለጡ ናቸው።

ለዚህ ችግር የሚያጋልጡ ምክንያቶች ፦
- የተለያዩ እንደ ሊድ ወይም እርሳስ ባሉ ማዕድናት የተበከለ አካባቢ መኖር፣
- በእርግዝና ወቅት መድኃኒቶች፣ አልኮል ወይም ሲጋራ / ትንባሆ ማጨስ ማዘውተር ሊሆኑ እንደሚችሉ ይገመታል።

ከዚህም በተጨማሪ በደም አማካኝነት በዘር የአእምሮ ህመሞችም ሊተላለፉ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።

ይህ የአእምሮ ችግር (ADHD) ያለባቸው ልጆች ቁጥር ለምን እንደጨመረ መንስኤውን ለማወቅ ጥናቶች እየተካሄዱ ነው።

#DeutscheWelle

@tikvahethiopia