TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ቲክቶክ

ካናዳ ከዛሬ ጀምሮ መንግሥት በገዛው ‘ኤሌክትሮኒክስ’ ቁሳቁስ #ቲክቶክ መጠቀም ክልል መሆኑን አሳውቃለች።

በዚህ ሳምንት መንግሥት ገዝቶ ለሠራተኞች ካደላቸው ተንቀሳቃሽ ስልኮች ውስጥ ቲክቶክ ይጠፋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ፤ መተግበሪያው ለመረጃ ደኅንነት አስጊ እንደሆነ ጠቋሚ ፍንጮች ስላሉ ነው ውሳኔው የተላለፈው ብለዋል።

የቲክቶክ ቃለ አቀባይ በካናዳ መንግሥት ውሳኔ ኩባንያው እንደተከፋ ገልጠዋል።

ቲክቶክ ይህን ውሳኔ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ የካናዳ መንግሥት ኩባንያውን ሳያማክር አሊያም በቂ ማስረጃ ሳይኖረው ይህን ማድረጉ አሳዛኝ መሆኑን ገልጧል።

* የአውሮፓ ኮሚሽን

ከቀናት በፊት የአውሮፓ ኮሚሽን ተመሳሳይ ውሳኔ አሳልፏል። የአውሮፓ ሕብረት ኮሚሽን ሠራተኞች ከመጋቢት 15 ጀምሮ ቲክቶክን በኮሚሽኑ ንብረት መጠቀም አይችሉም ሲል ነው ውሳኔ ያሳለፈው።

* አሜሪካ

ባለፈው የፈረጆቹ ዓመት የአሜሪካ የፌዴራሉ መንግሥት ሠራተኞች ቲክቶክን እንዳይጠቀሙ ተከልክለዋል።

ትላንት ዋይት ሐውስ የመንግሥት መ/ቤቶች በሚቀጥሉት 30 ቀናት ከኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎቻቸው ቲክቶክን #እንዲያስወግዱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

በርካታ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች መተግበሪያውን ከኔትዎርኮቻቸው ላይ አስወግደውታል።

* ሕንድ

ሕንድን ጨምሮ በሌሎች የእስያ ሃገራት የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በቲክቶክ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ እየወሰዱ ነው።

#ቲክቶክ

ቲክቶክ ባይትዳንስ የተሰኘው ኩባንያ ንብረት ነው።

መተግበሪያው ግላዊ መረጃን በመበዝበዝ ከፍተኛ ወቀሳ የሚደርስበት ሲሆን ከቻይና መንግሥት ጋር ግንኙነት አለው በሚልም ስሙ ይነሳል።

ኩባንያው የቻይና መንግሥት መረጃውን እንደማያገኝበትና ቻይና ያለው ቲክቶክ ከሌላው ዓለም ፈፅሞ የተለየ መሆኑን ደጋግሞ አሳውቋል።

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
“ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” - ስፔንሰር ኮክስ

የአሜሪካ ሀገር " ዩታህ ግዛት " በታዳጊዎች ፌስቡክ፣ ቲክቶክ እና ኢነስታግራምን የመሰሉ ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸው ላይ ገደብ ጣለች።

ይህ በማድረግ አሜሪካ ውስጥ የመጀመሪያዋ ግዛት ሆናለች።

ትላንት ሀሙስ በፀደቀው ደንብ መሰረት ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም#ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።

የፀደቀው ደንብ ምን ይዟል ?

- የማኅበራዊ ሚዲያ አገልግሎት አቅራቢ ኩባንያዎች ለልጆች አገልግሎቱን ከማቅረባቸው በፊት #የወላጆችን ይሁንታ ማግኘት ይኖርባቸዋል።

- ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጆቹ #ኢኒስታግራም#ፌስቡክ እና #ቲክቶክ ከመክፈቱ በፊት የወላጅ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል።

- ኩባንያዎች መተግበሪያዎቻቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ አዳጊዎች ያለ ወላጅ ይሁንታ እንዳይከፍቱ ያደረጋሉ።

- ኩባንያዎቹ የአዳጊዎቹን የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም፣ ታሪክ፣ የለጠፏቸውን እና በግል #የተጻጻፏቸውን_መልዕክቶች ሁሉ ለወላጆች መስጠት ይገደዳሉ።

- የማኅበራዊ ሚዲያ አቅራቢ ኩባንያዎች የልጆቹን ፍላጎት እና ምርጫ መሠረት አድርገው #ማስታወቂያ በልጆቹ የማኅበራዊ ሚዲያ ሰሌዳቸው ላይ እንዳይለቁ ይገደዳሉ።

- ታዳጊዎች ማኅበራዊ ትስስር መድረኮችን ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ንጋት 12፡30 ድረስ መጠቀም እንዳይችሉ ይደነግጋል።

ሕጉ ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው ከሚቀጥለው ዓመት መጋቢት ጀምሮ ነው።

ይህን እርምጃ መውሰድ ያስፈለገው ማኅበራዊ የትስስር መድረኮች በልጆች #የአእምሮ_ጤና ላይ ከፍ ያለ መረበሽን እያደረሱ መሆኑ ከተደረሰበት በኋላ ነው ተብሏል።

የዩታህ ግዛት ገዢ ስፔንሰር ኮክስ በትዊተር ገፃቸው ላይ ፤ “ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የልጆቻችንን አእምሮ እንዲበርዙ መፍቀድ የለብንም ” ሲሉ ጽፈዋል።

ከዩታህ በተጨማሪ ተመሳሳይ ሕጎች በቴክሳስ፣ በኦሃዮ፣ በአርካንሳስ፣ በኒው ጀርሲ እና በሊዊዚያና ግዛቶች እየተረቀቁ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።

Credit : #BBC

@tikvahethiopia
የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መልዕክት መለዋወጫ !

ከዚህ ቀደም ተከፍተው አገልግሎት ላይ የነበሩት የመልዕክት መቀበያዎች በተደጋጋሚ በቴሌግራም ቴክኒንክ ችግር አገልግሎታቸው እየተደነቃቀፈ ነው።

በዚህም ምክንያት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች የሚመጡትን መልዕክቶች ለማግኘት ችግር ሆኗል ፤ ለተፈጠረው ችግር ሁሉ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን።

ችግሩን ለመቅረፍ እና በየትኛውም መልኩ ነፃነቱ የተጠበቀ ለቲክቫህ አባላት ብቻ የሚያገለግል የሀሳብ መለዋወጫ በቅርቡ ይፋ የምናደርግ ሲሆን እስከዛው ድረስ ግን በዚህ አዲስ መልዕክት መቀበያ ላይ ብቻ መልዕክት ማጋራት ይቻላል  👉@tikvah_eth_BOT

በተጨማሪ @tikvah_Ethiopia_Fam ወይም ደግሞ 0703313630 መደወል ይቻላል።

በቲክቫህ ቤተሰብ ውስጥ ማስተላለፍ የሚቻሉ መልዕክቶች ምን አይነት ናቸው ?

- የፀጥታ ችግሮች፣ የደህንነት ስጋቶች፣ የወንጀል ድርጊቶች በመንግስት አካላት / ተቋማት የሚፈፀሙ ማንኛውም አይነት አስተዳዳራዊ በደሎች፤
- የየመንገድ ፣ የውሃ፣ እንዲሁም የኑሮ ውድነት፣ የኢኮኖሚና የሌሎችም መሰረታዊ ጥያቄዎች፤
- በግልም ሆነ በጋር የማያጋጥሙ ችግሮች፣ ሊበረታቱ የሚግባቸው ተግባራት፣
- ለሀገር እና ለትውልድ ጠቃሚ ናቸው የሚባሉ ሃሳቦችን፣
- የእርስ በእርስ እገዛዎች ፣ የበጎ አድራጎት ስራዎች፣
- ጥቆማዎችን ፣ ጥያቄዎችን ፣ ይሄ ነገር ለቤተሰቡ ቢጋራ መልካም ነው የምትሉትን (ዜና ፣ መረጃ) ሁሉ ማቅረብ ትችላላችሁ።

ምን መላክ አይቻልም ?

ስድብ፣ የጥላቻ ንግግር ፣ የማንኛውም የግለሰብ ማንነትን በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ የሚነካ ፣ ህዝብን በጅምላ የሚፈርጅ፣ ፣ ህዝብ ላይ ጥላቻን የሚያሰርፅ፣ ሀገር ሊያስጣ የእርስ በእርስ ግጭት የሚያባብስ፣ ሀሰተኛ መረጃ ፅሁፍ / መልዕክት መላክ በፍፁም አይቻልም። በየትኛውም አካል ላይ ትችትም ይሁን ቅሬታ ለመግለፅ የሚፈልግ የቤተሰቡ አባል የሚጠቀማቸውን ቃላት የመምረጥ ግዴታ አለበት።

ውድ ቤተሰቦቻችን ማንኛውም መልዕክት ስትልኩ የራሳችሁ የግላችሁ መልዕክት መሆኑን በማስረጃ አስደግፋችሁ ላኩልን። እናተ ያላረጋገጣችሁትንና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስላያችሁት የራሳችሁ በማስመሰል ማንኛውም መልዕልት መላክ ፍፁም አይቻልም።

ማስታወሻ ፦ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት #በፌስቡክ#ዩትዩብ#ቲክቶክ ላይ ምንም አይነት የመሰባሰቢያ መድረክ (ገፅ) የላቸውም።

ትዊተር ፦ https://twitter.com/tikvahethiopia?t=jZrpieALuIGzw6OM-HWgEw&s=09

ሀሳባችን ስንገልፅ ቃላትን እንምረጥ !!
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ!!
#TikvahFamily

@tikvah_eth_BOT
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
" ቲክቶክ " ኬንያ ውስጥ እንዲታገድ አቤቱታ ቀረበ።

የኬንያ ፓርላማ " #ቲክቶክ " የተሰኘው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ እንዲያግድ አቤቱታ እንደቀረበለት የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

" ወጣቶች ትምህርታቸውን ትተው የ 'ቲክቶክ' ቁራኛና የአዕምሮ ህመምተኛ እየሆኑ ነው " የሚለው አቤቱታው ፓርላማው አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ ጠይቋል።

የፓርላማው አፈጉባኤ ሞሰስ ዋታንጉላ፣ " ሁከትን እና የጥላቻ ንግግርን የሚያበረታቱ " እና " የብልግና " እና " መረን የለቀቀ ጾታዊ ይዘት " ያላቸው የ " ቲክቶክ " ተንቀሳቃሽ ምስሎች " በኬንያ ባሕላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶች ላይ አደጋ ደቅነዋል" በማለት አቤቱታውን ደግፈው መናገራቸው ተዘግቧል።

የኬንያ ፓርላማ በአቤቱታው ላይ ውሳኔ ባይሰጥም ፤ የመጀመሪያ ውይይት ግን እንዳደረገበት ተጠቁሟል።

ኬንያ በአፍሪካ በቲክቶክ ተጠቃሚዎች ብዛት ቀዳሚ ናት።

Credit : WazemaRadio
Video Credit : Citizen TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ " ኬንያ ውስጥ እንዲታገድ አቤቱታ ቀረበ። የኬንያ ፓርላማ " #ቲክቶክ " የተሰኘው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ እንዲያግድ አቤቱታ እንደቀረበለት የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። " ወጣቶች ትምህርታቸውን ትተው የ 'ቲክቶክ' ቁራኛና የአዕምሮ ህመምተኛ እየሆኑ ነው " የሚለው አቤቱታው ፓርላማው አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ ጠይቋል። የፓርላማው አፈጉባኤ ሞሰስ ዋታንጉላ፣ " ሁከትን እና የጥላቻ ንግግርን…
#ቲክቶክ

የኬንያ ፓርላማ " ቲክቶክ ይታገድ " የሚል አቤቱታ ከቀረበለት በኃላ የፓርላማው አፈጉባኤ በቲክቶክ " ሁከትንና የጥላቻ ንግግርና የሚያበረታቱ እንዲሁም የብልግና እና መረርን የለቀቁ ፆታዊ ይዘት ያላቸው ቪድዮዎች እየተሰራጩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶች ላይ አደጋ ደቅነዋል የሚለውን ሃሳባቸውን የተመለከቱ በርካታ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት " የኢትዮጵያ ሁኔታስ ? " በሚል አስተያየታቸውን በመልዕክት መቀበያ ልከዋል።

እንዚህ አስተያየቶች መተግበሪያው በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ ፦
- በከፍተኛ ደረጃ ወጣቱን የመተግበሪያው ሱሰኛ በማድረግ ፤
- ተማሪዎችን በማዘናጋት ፤
- በብሄር፣ በሃይማኖት ጥላቻ ስድብ እንዲበራከት
- የብልግና ንግግሮች እንዲስፋፉና እንዲለመዱ በማድረግ፣
- በእርዳታ ስም ማጭበርበሮች እንዲስፋፉ
- ከምንም በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ በህግም በሃይማኖትም ፍፁም አፀያፊ የሆነውን የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት እንዲስፋፋ በማድረግ በአንፃሩን ይህን የሚቃወሙ ወጣቶችን ከመተግበሪያው በማውረድ በሀገሪቱ ባህል እና ሃይማኖት ላይ ከፍተኛ አደጋ መደቀኑን አንስተዋል።

በአንፃሩ ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች መተግበሪያው የራሱ ጉድለቶች ቢኖሩትም ፦
- በርካታ ወጣቶች በመተግበሪያው ገንዘብ እንዲያገኙ በማድረግ ህይወታቸውን እንዲቀይሩ ፣
- ችሎታ ያላቸው ችሎታቸውን እንዲያጎለብቱና እንዲያስተዋውቁ በማድረግ፤
- ሚዲያ ያላገኙ ወጣቶች በአንድ ተንቀሳቃሽ ምስል ብቻ ብዙሃን ጋር እንዲደርሱ በማድረግ
- የታመሙ እንዲረዱ ፤ የተቸገሩ ወገኖች እንዲደረስላቸው ፣
- ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለወገናቸው ፣ ግድ የሚሰጣቸው ወጣቶች ድምፃቸው እንዲሰማ በማድረግ፣
- ፖለቲከኞች ፣አክቲቪስቶች የኔ የሚሉትን ወገን እንዲያነቁና ስለ ወቅታዊ ሁኔታ እንዲገነዘቡ በማድረግ፣
- በድካም የዛሉ ሰዎች በአሥቅኝ ቪድዮችን እንዲዝናኑ፣
- የውይይት ባህል፣ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ልምድ እንዲጎለብት በማድረግ
- ሃሳብ ኖሯቸው ተደራሽ ያልሆኑ ወጣቶችን በቀሉ በማስተዋወቅ ከፍተኛ በጎ አስተዋውፆ ማድረጉን አንስተዋል።

ይህን አስተያየቶች ከተመለከትን በኃላ ብዙሃኑ የመተግበሪያው ተጠቃሚ ምን ይላል ? ያሚለውን በግልፅ በይፋዊ መንገድ ለማወቅ Poll ያዘጋጀን ሲሆን ከታች ይለጠፋል👇

@tikvahethiopia
#USA

" ፕሬዜዳንት በሆንን በአንድ ሳምንት ውስጥ ቲክቶክን እናግዳለን " ያለቱ የሪፐብሊካን እጩዎች !

የአሜሪካ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ በ2024 ይካሄዳል።

የሪፐብሊካን የፕሬዜዳንታዊ እጩዎች ቢሮ በገቡ በመጀመሪያው ሳምንት " #ቲክቶክ " የተሰኘውን መተግበሪያ እንደሚያግዱ ገልጸዋል።

እጩዎቹ ሰሞኑን በነበረ ክርክር መድረክ ላይ ነው ይህን የገለፁት።

እጩዎች የቻይናን መረጃ መሰብሰብን ለመዋጋት አንዴ ፕሬዜዳንት ሆነው ወደ ነጩ ቤተመንግስት ይግቡ እንጂ " ቲክቶክ" ን እስከወዲያኛው እንደሚያግዱት ገልጸዋል።

ክሪስ ክርስቲ የተባሉ የሪፐብሊካን እጩ ምን አሉ ?

እኚህ እጩ " ቲክቶክ " መረጃዎችን ከመሰብሰብ ባለፈ በመላው ሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የወጣት አሜሪካውያንን አእምሮ እየበከለ ነው ብለዋል። " ይህንን የሚያደርጉት ደግሞ ሆን ብለው ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ቲክቶክ " በአልጎሪዝሙ አሰቃቂ፣ ያልተገቡ፣ ከፋፋይ፣ አፍራሽ ፣ የወጣቶችን አእምሮ የሚበክሉ ጉዳዮችን ከፍተኛ ደረጃ ወደ ተጠቃሚው እንዲገፋ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ይህም ቻይና አሜሪካንን ለመከፋፈል ይበልጥ እየተጠቀመችበት ያለ ተግባር ነው ሲሉ ከሰዋል።

የሪፐብሊካኑ ሰው የቀድሞው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስልጣን ዘመናቸው " ቲክቶክን ማገድ " በተመለከት ብዙ ሲናገሩ እንደነበር ነገር ግን መተግበሪያውን ማገድ ሲገባቸው ያን አለማድረጋቸው የሚያስወቅስ እንደሆነ ገልጸዋል።

እሳቸው ፕሬዜዳንት ሆነው በመጡ በመጀመሪያው ሳምንት ቲክቶክን እንደሚያግዱ አሳውቀዋል።

ሮን ዴሳንቲስ የተባሉ እጩ ደግሞ " የአሜሪካን ህዝብ ለመጠበቅ ስንል ቲክቶክን የማገድ እርምጃ እናሳያችኃለን " ብለዋል። ፕሬዜዳንት ሆነው ሲመጡም ይህንን እንደሚያደርጉትን ገልጸዋል።

ቲም ስኮት የተባሉት እጩ ፤ " እኛ ማድረግ ያለብን ቲክቶክን ማገድ ነው ፤ አለቀ !! " ብለዋል።

በቀድሞው ፕሬዝደንት ትራምፕ ቲክቶክን ለማገድ ሁለት ጊዜ ሲሞከር አይተናል ያለቱ ስኮት ፤ ነገርግን በፌደራል ፍርድ ቤቶቻችን እንዳይፈፀም ተደርጓል ሲል አስታውሰዋል።

ቲክቶክን ማገድ ካልተቻለ በመተግበሪያው ላይ ያለውን የቻይናን ተፅእኖ መኖር እንደወዲያኛው #ማስወገድ ነው ብለዋል።

ባይትዳንስ የተሰኘው ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " ከዚህ ቀደም በተለይም ግላዊ መረጃን በመበዝበዝ እና ከቻይና መንግሥት ጋር የተቆራኘ ነው በሚል ከፍተኛ ወቀሳ ሲደርስበት ነበር ፤ ኩባንያው የቻይና መንግሥት መረጃውን እንደማያገኝበትና ቻይና ያለው ቲክቶክ ከሌላው ዓለም ፈፅሞ የተለየ መሆኑን ደጋግሞ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሶማሊያ ሶማሊያ ቲክቶክ እና ቴሌግራም እንዲሁም 1ኤክስቤት (1XBet) የተባለውን የስፖርት ውርርድ ገጽን እንዲዘጉ አዘዘች። " ቲክቶክ " እና " ቴሌግራም " የአሸባሪዎች መረጃ ማስተላለፊያ ሆነዋል ብሏል የሶማሊያ መንግሥት። መተግበሪያዎቹ " አሸባሪ ድርጅቶች እና ቡድኖች አሰቃቂ የሆኑ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እንዲሁም ፎቶግራፎችን በማሰራጨት ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ጥቅም ላይ ውለዋል " ሲል ገልጿል።…
ኔፓል ሀገሪቱ ላይ " ቲክቶክ " እንዲታገድ ወሰነች።

ኔፓል ፤ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚረብሹና የቤተሰብን መዋቅር እንዲሁም ማህበራዊ ግንኙነቶችን የሚያውኩ ይዘቶችን ለማጋራት ጥቅም ላይ እየዋለ ነው ያለችውን የቻይናውን " #ቲክቶክ " መተግበሪያ እንዲታገድ ውሳኔ አሳለፈች።

ሀገሪቱ ፤ " ቲክቶክ " በማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ያለች ሲሆን በመተግበሪያው ላይ የሚለቀቁት ተንቀሳቃሽ ምስሎችና የሚተላለፉት መልዕክቶች ለሀገሪቱ ህዝብ ባሕል እንግዳ የሆኑና ቀድሞ በማህበረሰቡ ዘንድ የነበረውን ማህበራዊ መስተጋብር የሚሸረሸሩ ናቸው ስትል አሳውቃለች።

የመገናኛ ና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ሬካ ሻርማ ፤ የቲክቶክ ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ የሀገሪቱ ካቢኔ ተሰብስቦ መመክሩንና #ለማገድ ውሳኔ እንዳሳለፈ ይፋ አድርገል።

የቴሌኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን ኃላፊ የሆኑት ፑሩሾታም ካናል በሰጡት ቃል ፤ በኔፓል የሚገኙ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች " ቲክቶክ " ን እንዲዘጉ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል፡፡

አንዳንዶች መዝጋታቸውን ሌሎችም በቀጣይ እንደሚያደርጉት ጠቁመዋል።

" ቲክቶክ " የማህበራዊ ህይወት ላይ እያሳደረ ነው ከተባለው አሉታዊ ተፅእኖ በተጨማሪ በርካታ ከመተግበሪያው ጋር የተያያዙ የሳይበር ደኅንነት ወንጀሎች መመዝገባቸው ተመላክቷል።

የኔፓል መንግስት ተቃዋሚዎች ውሳኔው " ውጤታማነት ፣ ብስለት እና ኃላፊነት " የጎደለው ነው ሲሉ ተቃውመዋል።

አንድ የእገዳው ተቃዋሚ ፤ በሌሎችም ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ብዙ የማያስፈልጉ ነገሮች እንዳሉ አንስተው መደረግ ያለበት እነሱን መቆጣጠር ነው እንጂ መገደብ አይደለም ብለዋል።

ወደ አንድ ቢሊዮን የሚጠጉ ወርሃዊ ተጠቃሚዎች አሉት የሚባለው ታዋቂው የቪዲዮ ማጋሪያ መድረክ " ቲክቶክ " መረጃን በመበርበር እና በወጣቶች ላይ ጎጂ ተፅእኖ እያመጣነው በሚል ከዚህ ቀደም በአንዳንድ ሀገራት እገዳ ገጥሞታል።

አንዳንድ ሀገራት መተግበሪያው የቻይና መንግሥት መረጃ ለመበርበር ይጠቀምበታል በሚል ይተቹታል።

የቻይናው ባይትዳንስ ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " በቤጂንግ ቀጥተኛ ቁጥጥር ስር ነው እየተባለ የሚቀርቡበትን ክስና ትችቶችን በተደጋጋሚ #እንደማይቀበል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ኔፓል ሀገሪቱ ላይ " ቲክቶክ " እንዲታገድ ወሰነች። ኔፓል ፤ ማህበራዊ መስተጋብርን የሚረብሹና የቤተሰብን መዋቅር እንዲሁም ማህበራዊ ግንኙነቶችን የሚያውኩ ይዘቶችን ለማጋራት ጥቅም ላይ እየዋለ ነው ያለችውን የቻይናውን " #ቲክቶክ " መተግበሪያ እንዲታገድ ውሳኔ አሳለፈች። ሀገሪቱ ፤ " ቲክቶክ " በማህበራዊ መስተጋብር ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ያለች ሲሆን በመተግበሪያው ላይ የሚለቀቁት…
#ቲክቶክ

ለምንድነው ሀገራት " ቲክቶክ " ን ለማገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉት ?

ከቅርብ ወራት ወዲህ አሜሪካ፣ አውሮፓ፣ ካናዳ ያሉ የህግ አውጪዎች ከፀጥታ እና ደህንነት ስጋት ጋር በማያያዝ ግዙፉን የአጫጭር ቪድዮዎች ማጋሪያ " ቲክቶክ " ን ለማገድ / ለመገደብ የሚያደርጉትን ጥረት ማጠናከራቸውን ኒውዮርክ ታይምስ አስነብቧል።

ዋይትሃውስ እኤአ በፌብሩዋሪ 27 የፌዴራል  ኤጀንሲዎች አፕሊኬሽኑን ከመንግሥት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ላይ እንዲያጠፉ 30 ቀናት ሰጥቷቸው ነበር ፤ እንዲሁም ኒውዮርክን ጨምሮ የተለያዩ ከተሞች የመንግሥት ሰራተኞች " ቲክቶክ " ን እንዳያወርዱ ከልክለዋል።

በተጨማሪም ባይደን በሀገር ደረጃ ከሁሉም መሳሪያዎች ላይ መተግበሪያው እንዲታገድ እንዲያደርጉ የድጋፍ እንቅስቃሴዎች ነበሩ፤ አሁንም አሉ።

ለምንድነው መንግሥታት ቲክቶክን ለማገድ የሚንቀሳቀሱት ?

በተለይ ምእራባውያኑ ቀጥታ ጉዳዩን #ከቻይና ጋር ያገኛኙታል።

የምዕራቡ ዓለም የሕግ አውጪዎች እና ተቆጣጣሪዎች " ቲክቶክ " / ባለንብረቱ የባይትዳንስ የተጠቃሚ መረጃዎችን በቻይና መንግሥት እጅ እንዲገቡ ያደርጋል የሚል አቋም አላቸው።

ለዚህም እንደማያሳያ የሚያደርጉት የቻይና መንግሥት ለደህንነት ጉዳይ መረጃዎችን ለማሰባሰብ በሚስጥር ከቻይና ኩባንያዎች እና ዜጎች መረጃዎችን መውሰድ የሚያስችለው ህግ እንዳለው በመግለፅ ነው።

ቲክቶክ መሰል ክሶችን ለረጅም ጊዜ ውድቅ አድርጓል።

- ህንድ በ2020 ላይ ነው ያገደችው።
- የብሪታኒያ ፣ የፈረንሳይ፣ የኒውዝላንድ ፣ የአውስትራሊያ፣ ካናዳ #ፓርላማዎች ከአባላት ኦፊሴላዊ መሳሪያዎች እንዲታገድ አድርገዋል።
-  የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት በተመሳሳይ ከአባላት ኦፊሴላዊ መሳሪያዎች ላይ አግዷል። የወረደውንም አስጠፍቷል።
- ካናዳ የመንግሥት መሳሪያዎች ላይ እንዳይሰራ፣ የመንግሥት ሰራተኞችም እንዳያወርዱት አድርጋለች።
- የዴንማርክ መከላከያ ሰራዊት ሰራተኞቹ በሙሉ እንዳይጠቀሙ አድርጓል። ስልካቸው ላይ ተጭኖ የነበረውንም አስጠፍቷል።
- ኖርዌይ በመንግሥት ሰራተኞች ስልክ ላይ እንዳይሰራ አድርጋለች።

በተጨማሪ ፦

* አፍጋኒስታን #ወጣቶችን ከአጓጉል ነገር ለመጠበቅ በሚል 2022 ላይ አድግዳለች።

* ኪርጊስታን በዚህ ዓመት የሀገሪቱን ባህል ወግ እና ስርዓት እየበረዘው ፣ ለልጆች፣ ለወጣቶች የአእምሮ ጠንቅ ነው በማለት አድጋለች።

* ኔፓል እና ሶማሊያም እንዲሁ እንዲታገድ ከወሰኑ ሀገራት መካከል ናቸው።

አሜሪካ ለማገድ እያደረገች ያለችው እንቅስቃሴ አለ ?

ካለፈው ዓመት ህዳር ጀምሮ እጅግ በርካታ ግዛቶች " ቲክቶክ " ን  ከመንግስት መሳሪያዎች አግደዋል።

የዩኒቨርሲቲዎች ለምሳሌ ፦ እንደ ቴክሳስ ፣ ኦውበርን ፣ ቦይስ ስቴት ዩኒቨርሲቲዎች አፕሊኬሽኑ #በዋይፋይ እንዳይሰራ አድርገው አግደዋል።

አሜሪካ ውስጥ ከደህንነት ጋር በተያያዘ ብቻ ሳይሆን ቲክቶክ ሱስ የሚያሲዝ እንደሆነና ወጣቶችን እና ህፃናት ልጆችን አሉታዊ ተፅኖ ያሳድራል በሚል የሚከሱ ግዛቶችም አሉ።

ኮንግረሱ ቲክቶክ እንዲታገድ ይፈልጋል ? እንዲታገድ የሚፈልጉ የኮንግረሱ አባላት አሉ። (ከዚህ ቀደም የቀድሞው ፕሬዜዳንት ትራምፕ የማገድ እንቅስቃሴን እንዲቆም መደረጉ ይታወሳል)

ምንም እንኳን አሜሪካ ውስጥ በመንግሥት መሳሪያዎች ላይ እንዲሁም በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች ዋይፋይ ቲክቶክ ቢታገድም 150 ሚሊዮን ነው ተብሎ ከሚገመተው ተጠቃሚ ላይ እንዲታገድ ለማድረግ ረጅም ሂደት ሊጠይቅ እንደሚችል በዘርፉ ላይ ያሉ ፀሀፊዎች ይናገራሉ።

" ቲክቶክ " በየጊዜው የሚነሱበትን በተለይም የደህንነት እና የቁጥጥር ክሶች ውድቅ ሲያደርግ ቆይቷል።

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

" ተጠርጣሪው ከ50 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር ከእያንዳንዳቸው መቀበሉ ተረጋግጧል " - ፖሊስ

" ያለምንም ቅድመ ክፍያ ቪዛ እናስጨርሳለን ! " በሚል #ቲክቶክ በተሰኘው የማህበራዊ መገናኛ ዘዴ ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

" ያለምንም ቅድመ ክፍያ ወደ ተለያዩ ሀገራት ለሚጓዙ ሰዎች ቪዛ እናስጨርሳለን ! " እያለ በቲክቶክ ሲያጭበረብር የነበረው ይኸው ግለሰብ ከ25 በላይ የሚሆኑ ግለሰቦችን  በማጭበርበር ከ50 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር ከእያንዳንዳቸው መቀበሉ ተረጋግጧል።

በቲክቶክ ሀሰተኛ የግለሰቡ ማስታወቂያ የተጭበረበሩት አብዛኞች ወደ #ካናዳ ለመጓዝ ፍላጎት አሳይተው ከተጠርጣሪው ጋር የተገናኙ ናቸው።

" ያለምንም ቅድመ ክፍያ የቪዛ ፕሮሰስ እጨርሳለሁ " ቢልም ተበዳዮችን የተለያየ ቦታ እየቀያየረ እያገኛቸው  ቪዛ እንዳለቀላቸው እየነገረ እና ሌሎች ምክንያቶችን እየሰጠ ከእያንዳንዳቸው ከ50 ሺህ እስከ 600 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ ተቀብሏል።

ተጠርጣሪው የማታለል ወንጀል እየፈፀመ መሆኑ የታወቀው " ቪዛ አልቆልሃል " ተብሎ 600 ሺህ ብር የከፈለ አንድ ግለሰብ ወደ ካናዳ ሀገር ለመሄድ አየር መንገድ በተገኘበት ወቅት #ቪዛው_ሃሰተኛ መሆኑ ከተነገረው በኋላ ለፖሊስ በሰጠው ጥቆማ ነው፡፡

አሁን ላይ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ ክስ ተመስርቶበታል።

ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በህግ አግባብ ቤቱ ሲበረበር ሀሰተኛ ሰነዶች እና ሰነዶቹን ለማዘጋጀት ሲጠቀምባቸው የነበሩ ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ ያሳያል።

#AddisAbabaPoliceCommission

@tikvahethiopia
#ቲክቶክ

የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት " ቲክቶክ " የተሰኘውን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ሊያግድ የሚችል አዋጅ አጸደቀ።

አዋጁ የቻይናው #ባይትዳንስ_ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " በስድስት (6) ወራት ውስጥ አክሲዮኖችን #ለአሜሪካውያን ካልሸጠ በመላው አሜሪካ ይታገዳል ብሏል።

ይህ አዋጅ በሴኔቱ ጸድቆ በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ካልተፈረመበት ህግ ሆኖ ተፈጻሚ አይሆንም ተብሏል።

ፕሬዝዳንት ባይደን ግን የህግ መወሰኛ ምክርቤቱ (ሴኔቱ) አዋጁን ካጸደቀው ሳይውሉ ሳያድሩ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩበት ከዚህ ቀደም መግለፃቸው ተነግሯል።

ባይትዳንስ በአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጸደቀውን አዋጅ ተፈጻሚ ለማድረግ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ይሁንታ ማግኘት አለበት።

በዓለማቀፍ ደረጃ በወር ውስጥ ከ1 ቢሊየን በላይ ተጠቃሚዎችን ያፈራው " ቲክቶክ " በአሜሪካም ከ150 ሚሊየን በላይ ተጠቃሚዎች አሉት።

መተግበሪያው የግለሰቦችን ምስጢር ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል በሚል በአሜሪካ በመንግስት ተቋማት ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውል ታግዷል።

በአንዳንድ ግዛቶች ትምህርት ተቋማት እንዲሁ ወጣቶችን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እየመራ ነው በሚልም ታግዷል።

አሁን ደግሞ በመላው ሀገሪቲ ቲክቶክ ሊታገድ ይችላል በሚል በቲክቶክ ገንዘብ የሚሰሩ በርካታ አሜሪካውያን የአዋጁን መጽደቅ ተቃውመው አደባባይ መውጣታቸውን አል አይን ኒውስ ሮይተርስ እና ቢቢሲን ዋቢ በማደርግ አስነብቧል።

" ቲክቶክ " ምንም እንኳን አሜሪካ ውስጥ ከቻይና ጋር ተገናኝቶ በይበልጥ ከደህንነት ጋር በተያያዘ እንዲታገድ ግፊት ቢደረግም እንደ ኔፓል፣ ኪርጊስታን በመሳሰሉ ሀገራት ፦
- " የማህበራዊ ህይወትን እያወከ ነው "
- " ለወጣቶች እና ለልጆች አእምሮ ጠንቅ ነው "
- " ጎጂ የሆኑን ከሀገር ባህል እና እምነት ያፈነገጡ ተግባራት ይሰራጩበታል "
- " ሱስ በሚያሲዝ ይዘቱ ወጣቱ ትውልድ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እያደረሰ ነው " በሚሉና በሌሎች ምክንያቶች ታግዷል።

በተቃራኒው የ" ቲክቶክ " መተግበሪያ ባለቤት የሆነው ባይትዳንስ ድርጅት በመረጃና ደህንነር ጉዳይ ከቻይና ጋር ምንም የሚያያዘው ነገር እንደሌለ በተደጋጋሚ የገለጸ ሲሆን እገዳውን የሚቃወሙ በርካታቾች ደግሞ ለወጣቶች እየስራ እድል እየፈጠረ ነው ፤ ብዙ ሰዎች ያለ ብዙ ድካም ተደራሽ እንዲሆኑ እያደረገ ነው ፣ የሰዎችን ህይወት እየለወጠ ነው በሚል እገዳውን ይቃወሙታል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቲክቶክ የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት " ቲክቶክ " የተሰኘውን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ሊያግድ የሚችል አዋጅ አጸደቀ። አዋጁ የቻይናው #ባይትዳንስ_ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " በስድስት (6) ወራት ውስጥ አክሲዮኖችን #ለአሜሪካውያን ካልሸጠ በመላው አሜሪካ ይታገዳል ብሏል። ይህ አዋጅ በሴኔቱ ጸድቆ በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ካልተፈረመበት ህግ ሆኖ ተፈጻሚ አይሆንም ተብሏል። ፕሬዝዳንት…
#ቲክቶክ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዓለም ላይ ትልቅ ተፅእኖ የፈጠረው በቻይናው ባይትዳንስ ኩባንያ የሚተዳደረው " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ በአሉታዊም ይሁን አውንታዊ መንገድ ስሙ ይነሳል።

በቻይና ያለው የቲክቶክ ይዘት እና በተቀረው ዓለም ያለው ልዩነት አለው የሚሉም ብዙ ናቸው።

አንዳንድ ሀገራት ልጆች እና ወጣቶችን ከአጉል ባህል ለመጠበቅ በሚል በሙሉ ሲያግዱት ፣ አንዳንዶች ደግሞ ከደህንነት ጋር በተያያዘ ከመንግሥት ቁሳቁሶች ፣ ከመ/ቤቶች አግደዋል።

ለመሆኑ ቲክቶክ በቻይና እና በተቀረው ዓለም ይለያያል ?

ትሪስታን ሃሪስ ፤ የቀድሞው የጉግል ሰራተኛ እና ለማህበራዊ ሚዲያ ስነምግባር ተሟጋች ሲሆኑ ፤ በቻይና ያለው የቲክቶክ ይዘት እና በተቀረው ዓለም ያለው ይዘት ልዩነት አለው ባይ ናቸው።

ዶዪን የቻይናው ቲክቶክ ልጆችን / ትውልድ ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል።

" የመተግበሪያው ባለቤቶች ቴክኖሎጅ በልጆች እድገት ላይ ያለው ተጽዕኖ በደንብ አድርገው የተገነዘቡ ናቸው " የሚሉት እኚሁ የማህበራዊ ሚዲያ ስነምግባር ተሟጋች ፤ " በቲክቶክ የሀገር ውስጥ (ቻይና) ስሪታቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ፦
* በቤት ውስጥ ሊያደርጓቸው የሚችሏቸው የሳይንስ ሙከራዎችን፣
* የሳይንስ እና ሌሉች ሙዚየም ኤግዚቢቶችን
* የሀገር ፍቅር ቪዲዮዎችን፣
* ትምህርታዊ የሆኑ ቪዲዮዎችን ያሳያሉ " ብለዋል።

እንዲህም ሆኖ እራሱ በሀገሪቱ ያሉት ታዳጊዎች / ልጆች በቀን ውስጥ በቲክቶክ ላይ የሚያጠፉት ሰዓታቸው የተገደበ መሆኑንም አንስተዋል።

በዩኤስ እና ቻይና በታዳጊዎች ላይ አንድ የተደረገ ጥናት እንደነበር የሚያነሱት ተሟጋቹ ይኸውም " ወደፊት የምትፈልጉት የምኞት ስራ ምንድን ነው ? " የሚል እንደሆነ በዚህም ውጤቱ ፦
- በዩኤስ ውስጥ ቁጥር 1 የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪ፤
- በቻይና ደግሞ ቁጥር 1 #የጠፈር_ተመራማሪ የሚል እንደነበር ገልጸዋል።

ከዚህ ወራት በፊት የቲክቶክ ዋናው ስራ አፈፃሚ በአሜሪካ ኮንግረስ ቀርበ ጠንካራ ጥያቄ በቀረበባቸው ወቅት አንዱ የተነሳው ፤ በቻይና ያለው ቲክቶክ ለልጆች የሚያስተዋውቀው ፦
° ሳይንስ
° የሒሳብ / ሌሎች የትምህርት ቪድዮዎችን ነው ፤ የሚያዩበት / የሚቆዩበት ሰዓትም ገደብ አለው ዩኤስ ውስጥ ግን የሚገፉት ቪድዮዎች ልጆች ራሳቸውን እንዲጎዱ የሚያደርግ ነው ይህ ለምን ? የሚል ነበር።

ቲክቶክ ሱስ የማስያዝ አሰራር እንዳለው የሚያነሱ ሌሎች ባለሞያዎች የሰዎችን ስሜት በማንበበ ረጅም ጊዜ እዛ ላይ እንዲያሳልፉ ያደርጋል ባይ ናቸው።

ለታዳጊዎ/ልጆች ተብሎ የተለየ ስሪት ስለሌለው ይተቹታል።

በቲክቶክ ላይ የመቆያ ጊዜ እንደ #ፍላጎት እና ያልተገደበ መሆኑም በተለይ ለወላጆች ፈተና እንደሆነ ያነሳሉ።

ምንም እንኳን በተለይ #አሜሪካውያኑ እያደረሰ ነው የሚሉት የማህበራዊ ተፅዕኖው እንዳለ ሆኖ ከደህንነትና ከቻይና ጋር ባላቸው ሁኔታ እንዲታገድ ወይም ድርሻ #እንዲሸጥላቸው በይበልጥ ቢፈልጉም በርካቶች በትውልድ ላይ ቀውስ እየፈጠረ ነው ፣ ቁጥጥርም የለው በሚል እንዲታገድ / የይዘት ቁጥጥር እንዲደረግበት ይፈልጋሉ።

ከዚህ በተቃራኒው ቲክቶክ በዩኤስ ሆነ በሌላው ዓለም የበርካታ ወጣቶችን ህይወት በገንዘብ ቀይሯል።

በርካቶችን ለብዙሃን አስተዋውቋል። ብዙ ገንዘብ እንዲሰሩም አድርጓል። አልጎሪዝሙ በትንሽ ድካምና ስራ ሚሊዮኖች ጋር ማድረስ መቻሉ ሰዎች በአንድ ሌሊት ብቻ የዝና ማማ ላይ ቁጭ እንዲሉ አድርጓል።

ከደህንነት ጋር በተያያዘ ለሚነሱ ሰፊ ጉዳዮች አስተዳዳሪዎቹ የተጠቃሚዎችን ምንም መረጃ ለቻይና መንግሥት አሳልፈው እንደማይሰጡ ደጋግመው ተናግረዋል። ሌሎች ወቀሳዎችንም አጥብቀው ይሞግታሉ።

@tikvahethiopia
#TikTok #USAHouse

የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ተሰብስቦ ለዩክሬን ፣ ለእስራኤል እና ለሌሎች የባህር ማዶ የአሜሪካ አጋሮች የ95 ቢሊዮን ዶላር (5,419,427,000,000 ብር) የእርዳታ ጥቅል/ፓኬጅ ረቂቅ ሕግ አጽድቋል።

" ቲክቶክ " በአሜሪካ እንዲታገድም ድምጽ ሰጥቷል።

የተወካዮች ምክር ቤቱ በመጀመሪያ ድምፅ የሰጠው በ " #ቲክቶክ " ጉዳይ ሲሆን ባለቤትነቱ የባይትዳንስ የሆነው መተግበሪያ ለአሜሪካ ኩባንያ ካልተሸጠና ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት ካላቋረጠ በመላው አሜሪካ ውጤታማ በሆነ መንገድ #ለማገድ 360 ለ 58 በሆነ ድምጽ ረቂቅ ሕግ #አጽድቋል

" ቲክቶክ " በአሜሪካ ከ170 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች አሉት።

በመቀጠል ምክር ቤቱ ፦

➡️ ለዩክሬን 60.8 ቢሊዮን ዶላር (3,422,796,000,000 ብር)፤

➡️ ለእስራኤል 26.4 ቢሊዮን ዶላር  (1,483,211,600,000 ብር)፤

➡️ ለታይዋን እና ለኢንዶ ፓስፊክ ሀገራት  ' ቻይናን ለሚጋፈጡ ' የ8 ቢሊዮን ዶላር (456,372,800,000 ብር) የእርዳታ ድጋፍ በድምሩ የ95 ቢሊዮን ዶላር ጥቅል እርዳታ ረቂቅ ሕግ አጽድቋል።

የምክር ቤቱ አባላት የዩክሬን ድጋፍ ሲጸድቅ ፤ " ዩክሬን !! " እያሉ በመጮህ የሀገሪቱን ባንዲራ ሲያውለበልቡ ታይተዋል።

@thiqahEth @tikvahethiopia