TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa ➡️ " እህታችንን የጠለፋት ግለሰብ ወደ ፓሊስ እንዳንሄድ በእህታችን ህይወት እያስፈራራን ነው " - የተጠላፊዋ ውድነሽ ማቲዎስ ቤተሰቦች በእንባ የታጀበ መልእከት ➡️ " ቆየት ብዬ ዝርዝር መረጃ ሰጣችኃለሁ " - ፖሊስ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ነው። ስሟ ውድነሽ ማቲዮስ ይባላል። በቀን 28/07/2016 ቅዳሜ ምሽት ከቤት " ሰው ይጠራሻል " ተብላ እንደወጣች አልተመለሰችም። ቤተሰቦቿ…
#Update

➡️ " እንደተባለዉ ጠለፋ አለመፈጸሙን በማወቃችንና ቤተሰቦቿ  ተስማምተዉ ጉዳዩ ከህግ እጅ እንዲወጣ ስለፈለጉ ክትትላችንን አቋርጠናል " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ

➡️ " ጉዳዩ በሽምግልና መያዙን እንፈልገዋለን ቢሆንም ህግ አይግባ የሚለዉን የልጄ ቃል ከራሷ የመጣ ስለመሆኑ እጠራጠራለሁ " - አባት አቶ ማቲዎስ

ከሰሞኑ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክ ከተማ የሆነ ወድነሽ ማቲዮስ የተባለች ግለሰብ በድንገት ከቤት ተጠርታ እንደወጣች መቅረቷንና ቆይቶም መጠለፏ መታወቁን ተከትሎ ቤተሰቦች " ፖሊስ አስፈላጊውን ክትትል አድርጎ ልጃችን ይመልስልን " ማለታቸዉን ቲኪቫህ ኢትዮጵያ መዘገቡ  ይታወሳል።

ይሁንና ጉዳዩን እየተከታተለ የነበረው የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ " ጉዳዩ ጠለፋ ሳይሆን በገዛ ፍላጎቷ ያደረገችዉ መሆኑን ደርሸበታለሁ " በማለት ክትትሉን ማቆሙን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

" ቤተሰቦቿ እንደሚሉት ጠለፋ ሳይሆን በፍላጎት የተደረገ መሆኑንና አሁን ላይ ጉዳዩ በሽምግልና እነደተያዘ " የገለጸዉ የከተማዉ ፖሊስ የሽምግልና ሂደቱ ከልጅቱ በተጨማሪ የቤተሰብ ይሁንታ ማግኘቱንም ገልጿል።

የልጅቱ አባት የሆኑት አቶ ማቲዎስ በበኩላቸዉ ሁኔታዉ በሽምግልና መያዙ ቢያስደስታቸዉም  ልጃቸዉን በስልክ እንጅ በአካል አለማግኘታቸዉ አሁንም ልባቸዉ ዉስጥ ጥርጣሬ እንደፈጠረ ተናግረዋል።

" ህግ አይግባ የሚለዉን የልጄ ቃል ከራሷ የመጣ ስለመሆኑ እጠራጠራለሁ "ብለዋል።

በመሆኑም በሲዳማ ባህል መሰረት ሚያዚያ 17 የሚደረገው ሽምግልና የተደበቀዉን ሚስጥር እንደሚፈታዉና መፍትሄዉንም ያቀርባል ብለዉ እንደሚያስቡ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
🚨 #ዲላ 🚨

ዛሬ በዲላ ከተማ 10 ሠዓት ገዳማ ንፋስ ቀላቅሎ በዘነበው ከባድ ዝናብ #ሁለት የአንድ ቤተሰብ #ህጻናት ህይወታቸው አልፏል።

2 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ቀላል ጉዳት የደረሰባቸውም ሰዎች አሉ።

ንብረት ላይም ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ደርሷል።

በርካታ ዛፎች እና በርካታ የኤሌክትሪክ ፖሎች ወድቀዋል።

የኤሌክትሪክ ኃይልም ተቋርጧል።

ነዋሪው የኤሌክትሪክ ኃይል ተስተካክሎ ወደ ቦታው እስኪመለስ እንዲታገስና እራሱ ከተለያዩ አደጋዎች እንዲጠብቅ የከተማው አስተዳደር አደራ ብሏል።

@Tikvahethiopia
🚨BREAKING🚨

ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች።

ከዛሬ 12 ቀናት በፊት እስራኤል በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች ተገድለዋል።

እስራኤል ለግድያው ኃላፊነቱን ባትወስድም ኢራን እሷ እንደሆነች ነው የምታምነው። ይህን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት ቆይታለች። መዛት ብቻ ሳይሆን ዝግጅትም ስታደርግ ነበር።

እስራኤልም " እኔ እራሴን ለመከላከል ዝግጁ ነኝ " ስትል ከርማለች።

ገና የእስራኤል እና የፍልስጤም ሀማስ ጦርነት ይህ ነው የተባለ መቋጫ ባላገኘበት ሁኔታ ኢራን እና እስራኤል የለየለት ጦርነት ውስጥ ይገባሉ በሚል ፍራቻ ሀገራት ሲያስጨንቃቸው ቆይቷል።

እንደ አሜሪካ ያሉ የእስራኤል እጅግ ጠንካራ ወዳጅ ሀገራት ኢራንን " አርፈሽ ተቀመጪ ጥቃት እንዳትፈጽሚ " ሲሉ ሲያስጠነቅቁ ነበር።

ዛሬ ለሊቱን በተሰማው ዜና ግን ኢራን እንደዛተች አልቀረችም እስራኤልን በድሮን (ሰው አልባ አውሮፕላን) ማጥቃት ጀምራለች። የሚሳኤል ጥቃትም እንደሚኖር ኢራን ገልጻለች።

እስካሁን ድረስ ከ100 በላይ የድሮን ጥቃቶችን እንደሰነዘረች ተሰምቷል።

የእስራኤል ጦርም የኢራን ድሮኖች ወደ እስራኤል እየተላኩ መሆኑን አረጋግጧል።  በትንሹ ከ100 በላይ ድሮኖች የእስራኤል አየር ክልል ሳይደርሱ መከላከል እንደተቻለ ገልጿል።

የአሜሪካ ጦርም እስራኤልን እየተከላከለ ሲሆን እስራኤልን ለማጥቃት የተላኩ ድሮኖችን መቶ መጣሉን አመልክቷል። የዩኬ አየር ኃይልም እስራኤልን እንዲያጠቁ የተላኩ ድሮኖችን መቶ ጥሏል።

እስራኤል ለማንኛውም የኢራን ቀጥተኛ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት እንደተዘጋጀች አሳውቃለች።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌባኖስ ያለው ሄዝቦላህ በሰሜናዊ እስራኤል የሚሳኤል ጥቃት እየፈፀመ ሲሆን የየመኑ ሁቲ ደግሞ እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፍቷል።

More⬇️
https://publielectoral.lat/+LM-bJ8NzZMcxMjA8

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🚨BREAKING🚨 ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች። ከዛሬ 12 ቀናት በፊት እስራኤል በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች ተገድለዋል። እስራኤል ለግድያው ኃላፊነቱን ባትወስድም ኢራን እሷ እንደሆነች ነው የምታምነው። ይህን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት ቆይታለች። መዛት ብቻ ሳይሆን ዝግጅትም…
#UPDATE

ኢራን ለሊቱን እስራኤልን በድሮን ፣ በሚሳኤልና ሮኬቶች ስትደበድብ ከቆየች በኃላ " እስራኤልን የመቅጣቱ ተግባር #ተጠናቋል " ብላለች።

እስራኤል ማንኛውም አፀፋዊ ምላሽ ሰጣለሁ ካለች ግን ከአሁኑ እጅግ በጣም የከፋው ቅጣት ይጠብቃታል ሲትል አስጠንቅቃለች።

ኢራን የትኛውም ህዝባዊ ይሁን ኢኮኖሚያዊ ዒላማዋች እንዳልነበሯት ዒላማዋ የእስራኤል ወታደራዊ ስፍራዎችና አቅም ላይ እንደነበር ገልጻለች።

ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በእስራኤል ላይ እንዲህ ያለውም ቀጥተኛ መጠነ ሰፊ ጥቃት የከፈተችው።

ከ360 በላይ ሚሳኤል እና ድሮኖች ከኢራን፣ ኢራቅ፣ የመን ወደ እስራኤል መወንጨፋቸውን የእስራኤል ሠራዊት አስታውቋል።

አብዛኞቹ ጉዳት ሳያደርሱ (99%) በእስራኤል እና በወዳጆቿ አማካይነት እንዲከሽፉ መደረጋቸው ተገልጿል።

ያም ሆኑ በጥቃቱ መጠነኛ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።

እስራኤል የለሊቱን ጥቃት ብቻ ለመመከት 1 ቢሊዮን ዶላር ሳታወጣ አልቀረችም ተብሏል።

የአሜሪካ ጦር በርካታ ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን ከአየር ላይ እንዲከሽፉ አድርጓል። ፕሬዜዳንቷም " እስራኤል የኢራንን ጥቃት የመከተችው በአሜሪካ ድጋፍ ነው " ብለዋል።

ዩናይትድ ኪንግደም እና ፈረንሳይም ከጥቃቱ በፊት የአየር ቅኝት በማድረግ እስራኤልን ሲያግዙ አንግተዋል።

ጆርዳን በአየር ክልሏ ሲያልፉ የነበሩ ድሮኖችን እየመታች የጣለች ሲሆን ይህንን " ለህዝቤ ደህንነት ስል ያደረኩት ነው " ብላለች።

ኢራንም ጆርዳንን " አርፈሽ ካልተቀመጥሽ አንቺም ልክ እንደ እስራኤል ትመቻለሽ " ስትል ዝታባታለች።

እስራኤል በቀጣይ የአፀፋ እርምጃ ትወስድ ይሆን ? የሚለው ብዙዎችን ያሳሰበ ጉዳይ ሲሆን " አሜሪካ ተያት አፀፋ አትውሰጂ " ብላታለች።

ቀድሞኑ በእራኤል እና ፍልስጤም ሀማስ  ጦርነት የተለያየ አቋም ያላቸው የተለያዩ ሀገራትና ተቋማት በጉዳዩ ላይ ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል። ውጥረቱ ይረግብ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢራን ፥ እስራኤልን የደበደበችው ከዛሬ 13 ቀን በፊት በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እስራኤል እንደፈፀመችው በምታምነው የአየር ጥቃት ከፍተኛ ጄኔራሏን ጨምሮ አጠቃላይ 13 ሰዎች በመገደላቸው ለሱ አፀፋ ነው።

መረጃው ከዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች የተሰባሰበ ነው።

More⬇️
https://publielectoral.lat/+LM-bJ8NzZMcxMjA8

@tikvahethiopia
#DStvEthiopia

የሳምንቱ ምርጥ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ💥
⚽️ አርሰናል ከ አስቶን ቪላ ጋር የሚያደርጉትን የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ፍልሚያ ዛሬ ከምሽቱ 12፡30 በቀጥታ በበዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ!

🤔 ኡናይ ኤምሪ የቀድሞ ቡድኑን ማሸነፍ ይችላል? አርሰናል የሊጉ መሪ ሆኖ መቀጠል ይችላል?

👉 የፕሮግራም መቋረጥ እንዳያጋጥምዎ የአገልግሎት ክፍያዎን ቀድመው ይፈፅሙ። ክፍያ ሲፈፅሙ ዲኮደሩ መብራቱን ያረጋግጡ።

👉 የዲኤስቲቪን ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!https://bit.ly/2WDuBLk

#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ከተጎጂዎች መካከል 30,427 ህፃናት ናቸው። የሟቾች ቁጥር ከ40 በላይ ደርሷል ” - ሴቭ ዘ ቺልድረን በሶማሌ ክልል ከተከሰተ የወራት ያለፈው የጎርፍ አደጋ የውሃ መጠኑ እየቀነሰ የመጣ ቢሆንም ትንበያዎች የሚያመለክቱት በመጪው የዝናብ ወቅት ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት እንዲሚችል ስለሆነ፣ ህብረተሰቡም አሁንም ካለፈው የጎርፍ አደጋ ገና እያገገመ በመሆኑ፣ ትልቅ ፈተናና ስጋት መፍጠሩን በቦታው የሚገኘው…
#SavetheChildren

“ በሚያሳዝን ሁኔታ 70 ሰዎች በኮሌራ ሕይወታቸውን አጥተዋል። 9 ሰዎች በኩፍኝ ሞተዋል ” - የህጻናት አድን ድርጅት

በሶማሌ ክልል በተለይም #የጎርፍ_አደጋ በደረሰባቸው ወረዳዎች በተፈናቀሉ ወገኖች የተከሰተ የኮሌራ ወረርሽኝ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሆነ የክልሉ የህጻናት አድን ድርጅት (Save the children) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የድርጅቱ ምሥራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ አብዲራዛቅ አህመድ ፣ የኮሌራ ወረርሽኙ እንደቀጠለ መሆኑን በሴፕተምበር 2023 ወረርሽኙ ከተከሰተ ጀምሮ በድምሩ 7, 480 ሰዎች እንደተጎዱ ገልጸዋል።

ዳይሬክተሩ በሰጡት ቃል፣ “ በሚያሳዝን ሁኔታ 70 ሰዎች በኮሌራ ሕይወታቸውን አጥተዋል። 9 ሰዎች ደግሞ በኩፍኝ ሞተዋል ” ብለዋል።

በተጨማሪም ከ2024 መጀመሪያ ጀምሮ 533 ሰዎች በኩፍኝ በሽታ እንደተያዙ፣ 9ኙ ሰዎች ለሞት የተዳረጉት በጎዴ ከተማ፣ ጎዴ ወረዳ፣ በራኖ አካባቢዎች መሆኑን አስረድተዋል።

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ምንድናቸው ?

📣 በጎርፍ ለተጎዳ ማህበረሰብ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚደረግ ምላሽ፣ የአደጋ ጊዜ መጠለያ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ ለማደረግ አቅርቦቶችን ማጎልበት። የኮሌራ ክትባቶች ከፍተኛ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ላሉ የህብረተሰብ ክፍሎች መስጠት ይገባል።

📣 የጎርፍ መጥለቅለቅ፣ መሠረታዊ እና አስፈላጊ የጤና አገልግሎቶችን ለማቅረብ ወሳኝ በሆኑ የጤና ተቋማት ላይ ጉዳት እንዳደረሰ በመገንዘብ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የጤና መሠረተ ልማት ግንባታ ላይ መዋዕለ ነዋይ ሊፈስ ይገባል።

📣 #ህፃናት በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሆናቸው ልዩ እንክብካቤ ያስፈልጋቸዋል። 

#ጥሪ

(አቶ አብዲራዛቅ አህመድ)

" ለለጋሽ ማህበረሰቡ አንድ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ። ወረርሽኝ እና ተደጋጋሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ የሚያመጣውን ከፍተኛ ጉዳትና ተጽዕኖ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመቀነስ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋል። "

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" ከባድ ተሽከርካሪዎች፣ ትራክተኖችና ማሽነሪዎችን እንዳናስገባ ተከልክለናል " - አስመጪዎች

ከባድ ተሽከርካሪዎችን ፣ ትራክተሮችን እና ማሽነሪዎችን ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ አስመጪዎች ፣ መንግሥት ምንም ዓይነት መመርያ ሳያወጣ ማስገባት አትችሉም በመባላቸው በሥራቸው ላይ እንቅፋት መፈጠሩን ተናገሩ።

አስመጪዎቹ ይህን የተናገሩት ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ነው።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያለ ምንም በቂ ምክንያት " የመኪና ማስገቢያ ፈቃድ አልሰጣችሁም " እንዳላቸው ገልጸው ጉዳዩን ፦ 
- ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣
- ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣
- ለገንዘብ ሚኒስቴርና ለጉምሩክ ኮሚሽን በአካል ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

ከዚህ በፊት በነዳጅ የሚሠሩ አውቶሞቢሎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከሉን መስማታቸውን ያስታወሱት አስመጪዎቹ፣ አውቶሞቢሎች እንዳይገቡ የተከለከለበት ዋነኛ ምክንያት እንደ አማራጭ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሠሩ ተሸከርካሪዎችን ማስገባት እንደሚቻል በማመን ነው ብለዋል፡፡

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከባድ ተሸከርካሪዎችንና ትራክተሮችን ማስገባት አትችሉም ካለ ከሳምንት በላይ እንደሆነ ገልጸዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ለተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ቅሬታቸውን በአካል ሲያስረዱ፣ ተቋማቱም እንዲህ ዓይነት መመርያ አለመኖሩን እንደገለጹላቸው ተናግረዋል።

ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤትን ጠይቁ መባላቸውን አመልክተዋል።

ክልከላው ሥራ ላይ እንቅፋት እንደፈጠረባቸውና የተለያዩ ተሽከርካሪዎችንም ሆነ ትራክተሮችን የሚሸጡ ነጋዴዎች ዋጋ ጨምረው በመሸጥ ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

አስመጪዎቹ ፥ ከባድ ተሽከርካሪዎችና ትራክተሮችን ጨምሮ ሌሎች ተሽከርካሪዎች እንደ አውቶሞቢሎች በኤሌክትሪክ እንደማይሠሩ ተናግረው  " ችግሩን መንግሥት በአፋጣኝ በመረዳት ክልከላው ሊያነሳልን ይገባል  " ብለዋል፡፡

መንግሥት ከባድ ተሽከርካሪዎች ሆነ ትራክተሮች በመመርያ ቢከለክል በአገር የመጣ ጉዳይ መሆኑን በማመን ሌላ አማራጭ እንደሚፈልጉ የገለጹት አስመጪዎቹ ችግሩን የፈጠረው አንድ የመንግሥት ተቋም መሆኑ ሁኔታውን የተወሳሰበ እንዲሆን አድርጎታል በማለት አስረድተዋል።

ሪፖርተር ጋዜጣ ፥ ጉዳዩን በተመለከተ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን በስልክ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም ሳይሳካ እንደቀረ አመልክቷል። #ሪፖርተርጋዜጣ

@tikvahethiopia
" እውቀቱ ሳይኖራቸው ቤተክርስቲያንን ወክሎ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ማስተላለፍ አይገባም " - ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፥ የዲጀታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ የራሷን ሕግና መመሪያ እንደምታዘጋጅ አሳወቀች።

ይህ የተሰማው " ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን " በሚል በቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መመሪያ በተዘጋጀ ሥልጠና ላይ ነው።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፥ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት እና ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ባለማስተላለፍ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

" ቤተክርስቲያንን ሳያውቁ ተገቢው ሙያና እውቀት ሳይኖራቸው የሃይማኖት አስተምህሮ ለማስተላለፍ እና በየማኅበራዊ ሚዲያው እና ዲጂታል ሚዲያው ለመንቀሳቀስ የሚሞክሩ አሉ " ሲሉ የጠቆሙት ብፁዕነታቸው " እውቀቱ ሳይኖራቸው ቤተክርስቲያንን ወክሎ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ ማስተላለፍ አይገባም " ሲሉ አሳስበዋል።

" ማኅበራዊ ሚዲያውና ዲጀታል ሚዲያው  ከቤተክርስቲያን ይልቅ ለግለሰቦች እና ለቡድን ፍላጎቶች የመቆም ዝንባሌ በሰፊው ይታያል " ያሉ ሲሆን " ቅድሚያ ለቤተክርስቲያን መስጠት ይገባል ፤ ገንዘብ መስብሰብን ዓላማ ያደረገ የዲጂታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ ሥራ በመንፈሳዊ ቅኝት ያልተቃኘ በመሆኑ እርምት የሚሻ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ብፁዕነታቸው በዲጂታል ሚዲያ እና ማኅበራዊ ሚዲያ የሚያገለግሉ እና የሚገለግሉ የቤተክርስቲኒቱ ልጆች ለቤተክርስቲያን ከማይጠቅሙ አጀንዳዎች ራሳቸውን እንዲያርቁ መክረዋል።

በዲጂታል ሚዲያና ማኅበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም በሕሙማን እና በቤተክርስቲያን ስም የሚከናወኑ ልመናዎች ለተባለው ዓላማ ስለመዋላቸው ማረጋገጥ ከእያንዳንዱ እርዳታ ሰጪ ይጠበቃል ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን በጣስ መልኩ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ በዲጂታል ሚዲያ የሚያስተላልፉ አገልጋዮች እና ሌሎች የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው አስጠንቅቀዋል።

" በቀጣይ የዲጀታል ሚዲያና ማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በተመለከተ የቤተክርስቲያኗ የራሷን ሕግና መመሪያ እንዲዘጋጅ ይደረጋል " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia