TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ገንዘብ #አጭበርባሪዎች ጥቆማ!

TechTalk With Solomon⬇️

"ገንዘብ #አጭበርባሪዎች ጥቆማ! በርካቶች በኢትዮጵያ እና በሌላም ቦታ ያሉ ሰዎች "እኛ አናደርግላችኋለን" በሚሉ አጭበርባሪዎች በኩል #የቢትኮይን ኢንቨስትመንት ውስጥ እየገቡ እንዳለ እየተነገረኝ ነው! አንድ ጠቃሚ ምክር ልስጣችሁ፤ ማንም ሰው ወደናንተ ቀርቦ ሃብታም አደርጋችኋለሁ እያለ ለፍታችሁ የሰራችሁትን ገንዘብ ለዚህ ጉዳይ ቢጠይቃችሁ ፍጹም እንዳታረጉት! ይህ በአሁን ሰዓት እየተበራከተ ያለ ወንጀል/#ማጭበርበር ነው።

"ሰዎች ብር ሲሰሩ እያየሁ ነው" ትሉ ይሆናል። ይህ አይነት ወንጀል #ከክሪፕቶከረንሲ በፊትም የነበረ ሲሆን፣ ነገሩ እንዲህ ነው -በኢንቨስትመንት ዓለም የሚታወት አንድ አደገኛ ወንጀል አለ "ፖንዚ ስኪም" ይባላል። ይህ ማለት ገንዘባችሁን በናንተ ስም ኢንቨስት አድርጌ #ትርፍ አመጣላችኋለሁ የሚለው አካል አብዛኛውን ገንዘብ ራሱ ከበላ በኋላ፣ ከአዲሲሶቹ ተጠቂዎች የሰበሰውን ለበፊቶቹ ተጠቂዎች በመስጠት በእርግጥ ትርፍ እያስገኘ እንዳለ ማስመሰል ነው። ከዚህ ወንጀል በጣም በጣም በጣም ተጠበቁ!

ክሪፕቶከረንሲ ላይ እጅግ በመጠኑ ኢንቨስት ማድረግ ከተፈለገ (አሁን ብዙም ባይመከርም) በትክክለኛ ሁኔታ እና በታወቁ አፖች (መተግበሪያዎች) በራሳችሁ ማድረግ ትችላላችሁ (ችግሩ በኢትዮጵያ የባንክ ካርድ አሰራር ማነስ እና እነዚህ አፖች ምናልባትም በኢትዮጵያ ላይሰሩ መቻላቸው ነው)"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጠንቀቁ ⚠️ ከኦንላይ ዘራፊና አጭበርባሪዎች እራሳችሁን ጠብቁ። ነገሩ እንዲህ ነው ... ገንዘባቸውን ኦንላይን ተጭበርብረው የተበሉ ግለሰቦች መጀመሪያ በማያወቁት የውጭ ሀገር ስልክ ቁጥር በ #ዋትስአፕ / በ #ቴሌግራም መልዕክት ይደርሳቸዋል። ስልካቸውን / username እንዴት እንደሚያገኙት ባይታወቅም። የሚደርሳቸው መልዕክት " ጥሩ የስራ እድል እንደሆነ ፣ በትንሽ ስራም ብዙ ትርፍ እንደሚያገኙ…
#ScamAlert

በርካታ ሰዎች አሁንም በኦንላንይን #አጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን የተጭበረበሩ ይገኛሉ።

ዛሬ እንዲሁም ትላንትና " #ተዘረፍን " ሲሉ መልዕክት የላኩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በዋስትስአፕ እና በቴሌግራም  ያነገሯቸው ሰዎች ፤ " ቀለል ያለ ስራ ስሩና ትርፋማ ሁኑ " በማለት ከ150,000 ብር በላይ እንዲልኩላቸው ካደረጉ በኃላ ሰዎቹ የውሃ ሽታ ሆነዋል።

" በእኛ የደረሰ በናተ እንዳይደርስ ለማንም የማታውቁት ሰው መልዕክት አትመልሱ ፤ እንዲሁ ቁጭ ተብሎ ምንም ሳይደክሙ ብቻ ትርፋማ መሆን አይቻልምና ገንዘባችሁ እንዳትበሉ " ብለዋል።

በድጋሚ ማኛውም የማታውቁት ሰው በቴሌግራም ፣ ዋትስአፕ፣ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም ላይ " ትርፋማ ስራ እናሰራችሁ " ወይም ሌላም መልዕክት ሲልክላችሁ አትመልሱ።

ሌላው የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ እና ሌሎች የመገልገያ እቃዎችን " #በርካሽ እንሸጥላችኃለን ቅድሚያ የሂሳቡን ግማሽ ላኩ " ለሚሏችሁም ሰዎች መልስ አትስጧቸው / እቃውን ይላኩና ገንዘቡን ላኩላቸው።

አንድ የቤተሰባችን አባል " አዲሱን አይፎን 15 ስልክ ከአሜሪካ በርካሽ እንልክልሃለን ቅድሚያ ግን ግማሹን አስገባ " በማለት 50 ሺህ ብር ካስላኩት በኃላ አድራሻቸውን አጠፋፍተዋል።

ከዚህም ባለፈ ደግሞ ወደ ውጭ ሀገራት ለትምህርት ለስራ እንላካችሁ የሚሉም በዝተዋልና አድራሻሸውን ፣ ህጋዊናታቸውን አጣሩ። በቅድሚያ ምንም አይነት ክፍያ እንዳትከፍላቸው። " ቅድመ ክፍያ የለውም " ካሉም በኃላ በተለያየ መንገድ ጉዳይ መጨረሻ በሚል የሚበዘብዙ አሉና ተጠንቀቁ።

@tikvahethiopia