TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፊቼ_ጨምበላላ

የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምበላላ በዓል ያለምንም የጸጥታ ስጋት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ገለጸ፡፡

ቢሮው 1 ሺህ 500 ወጣቶች ከጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አሳውቋል።

የፊቼ ጨምበላላ በዓል ከሲዳማ አልፎ የአለም ቅርስ በመሆኑ በዓሉ ባህልና እሴቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ ቀዳሚ ስራው መሆኑን ቢሮው ገልጿል።

ለስራው መሳካት ብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተቋም ከሁሉም የፌዴራልና የሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ጋር በጋራ ሰፊ ስራ እየሰሩ መቆየታቸውን እና ተግባሩ እስከ በዓሉ መባቻ ድረስ እንደሚዘልቅ ተገልጿል።

ለሰላም መጠበቅ የህብረተሰቡ ሚና ግንባር ቀደም ቦታ እንዳለው የተግለፀ ሲሆን ማንኛውም አጠራጣሪ ነገር ከተመለከቱ በቶሎ በአቅራቢያቸው ላሉ የጸጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡም ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ፦ ደሬቴድ

@tikvahethiopia
#ፊቼ_ጨምበላላ

የሲዳማ የዘመን መለወጫ የፊቼ ጨምባላላ በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ዛሬ በዓሉ በሲምፖዚየምና ሌሎች ዝግጅቶች በሀዋሳ ተከብሯል።

በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደው ሲምፖዚየም ላይ የፊቼ ጫምባላላ ባህላዊ እሴቶች ዙሪያ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርቧል።

በዛሬው የበዓሉ ዋዜማ  የ ”ሻፌታ” ሥነ-ሥርዓትን ጨምሮ ሌሎችም  ዝግጅቶች  ነበሩ።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳና የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ሰርሞሎና የዞን አመራሮች ተገኝተው ነበር።

በተጨማሪ የመጀመሪያው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አባተ ኪሾ፣ አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤና አምባሳደር ደሴ ዳልኬ ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ታድመው እንደነበር ከኢዜአ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia