TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
መንግሥት የከለከለው ሰልፍ ... በሳምንቱ መጀመሪያ ሰኞ በአደባባይ ሊከበር የነበረው የሰራተኞች በዓል (ሜይዴይ) በመንግስት መከልከሉ ይታወሳል። በዚህ ዙርያ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ምን አሉ ? አቶ ካሳሁን ፎሎ ፦ " የእኛ አላማ የነበረው የሰራተኛውን ጥያቄ ይዘን በመላው ከተማ ሳይሆን በመስቀል አደባባይ ብቻ ማክበር እና ጥያቄዎቻችንን በሰላም ማቅረብ…
#Update

ዛሬ ከሰዓት የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር " መልካም የሥራ ግንኙነት ስለመፍጠር " መወያየታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ውይይቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አንገብጋቢ ባላቸው የሠራተኞች ጥያቄዎች ላይ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድን አግኝቶ ማነጋገር #ግድ እና #ብቸኛ አማራጭ መሆኑን ገልጾ ነበር።

ኮንፌዴሬሽኑ ዘንድሮ የሜይ ዴይ በዓል ላይ በአዲስ አበባ ከተማ በአደባባይ ሊያነሳቸው የነበሩ ጥቄያዎች ሰልፍ እንዳያደርግ በመከልከሉ ጥያቄዎቹን ሳያቀርብ እንደቀረ ይታወሳል።

በኃላ ሊያነሳቸው የነበረውን ጥያቄዎችን በማካተት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በጻፈው ደብዳቤ፣ እሳቸውን ማነጋገር ለሠራተኞች ጥያቄዎች ምላሽ ለማግኘት እንደሚረዳ ገልጾ ነበር።

በወቅቱ በፃፈው ደብዳቤ በየጊዜው እያሻቀበ በመጣው የኑሮ ውድነት፣ የኢትዮጵያ ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸው መኖር የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ገልጾ ለዚህ ብቸኛው መፍትሄው ጠቅላይ ሚኒስትሩን  አግኝቶ ማነጋገር እንደሆነ ገልጿል።

ኢሠማኮ የሠራተኞች አንገብጋቢ የሚባሉ ጥያቄዎችን አስመልክቶ በተለያዩ መንገዶች ለሚመለከታቸው መንግሥታዊ አካላት ጥያቄ ቢያቀርብም፣ ምላሽ ሊያገኝ እንዳልቻለ በዛው ደብዳቤ ተመላክቷል።

ከዚህ ቀደም የሠራተኞች ጥያቄ የቀረበላቸው መንግሥታዊ አካላት ጥያቄውን ወደ ጎን የመግፋት አዝማሚያ እያሳዩ በመምጣታቸው፣ የኢሠማኮ አመራር " ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአነጋግሩን " ጥያቄ ለማቅረብ መገደዱን በወቅቱ በፃፈላቸው ደብዳቤው አስረድቶ ነበር።

#ማስታወሻ

ከዚህ ቀደም ኢሠማኮ ከሰራተኛው ጥያቄ ጋር በተያያዘ እንዳያደርግ በተከለከለው ሰልፍ ሊጠይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎች ምን ነበሩ ?

1. በከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሰራተኛው እየተቸገረ ነው፣ በተለይ ደግሞ ደሞዝ ተከፋዩ። መንግስት መፍትሄ ይስጠን። አብዛኛው ሰራተኛ በቀን አንዴም ለመብላት እየተቸገረ ነዉ።

2. የስራ ግብር ይቀነስልን።

3. የዛሬ አራት አመት ወጥቶ የነበረው የዝቅተኛ ደሞዝ ማስተካከያ አዋጅ እስካሁን ደንብ ሳይወጣለት ቆይቷል። ይህም ትኩረት ይሰጠው፣ በ600 ብር እየኖረ ያለ ሰው አለ፣ ኢንደስትሪ ፓርኮች ውስጥ ደሞዝ በአማካኝ ከ800 - 1,200 ብር ነው።

4. የአሰሪና ሰራተኛ ኤጀንሲዎች ከደምበኛቸው ከሚቀበሉት ክፍያ ለሰራተኛው 80 ፐርሰንት ከፍለዉ ቀሪውን 20 ፐርሰንት እንዲወስዱ በሚል የወጣዉ መመሪያ አለመከበር በኤጀንሲ በተቀጠሩ  ሰራተኞች ላይ ተመልካች ያጣ የጉልበት ብዝበዛ እየተካሄደ ነው፣ መንግስት ትኩረት ያርግበት የሚል ነው።

@tikvahethiopia
በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረቡትን የሳፋሪኮም ቲክቶክ ጥቅሎችን በመጠቀም አዳዲስ ቪዲዮዎችን እየሰራን ለምንወዳቸው ሰዎች እንላክ፣ ዘና ፈታ እንበል!

አሁኑኑ ወደ *777# በመደወል ጥቅላችንን እንግዛ!

#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " - የጋቦን ወታደሮች በጋቦን መፈንቅለ መንግሥት ተደረገ። ባሳለፍነው ቅዳሜ በአፍሪካዊቷ ሀገር ጋቦን ምርጫ ተደርጎ ነበር በዚህም ምርጫ ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር። ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮችየተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን መቆጣጠራቸውን አሳውቀዋል። በአገሪቱ…
#Update

የጋቦን ወታደሮች አሊ ቦንጎን የቤት ውስጥ እስረኛ አድርገዋቸዋል።

መፈንቅለ መንግሥት የተደረገባቸው ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ካሉበት ቤት ውስጥ ሆነው " እርዱኝ " የሚል ይዘት ያለው መልዕክት ለወዳጆቻቸው በቪድዮ አሰራጭተዋል።

ምንጩ በትክክል ባልታወቀውና በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰጨው ቪድዮ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ " በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ሁሉ ድምፅ እንዲያሱም " ተማፅነዋል።

" እዚህ ያሉ ሰዎች እኔን እና ቤተሰቦቼን አስረዋል ፤ ልጄ የሆነ ቦታነው ያለው፤ ባለቤቴ ሌላ ቦታ ነች ፤ እኔ ደግሞ አሁን ያለሁት በመኖሪያ ቤቴ ውስጥ ነው። ምንም እየተፈጠረ አይደለም ፤ ምን እየሆነ እንዳለም አላውቅም። " ብለዋል።

በመሆኑም በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ድምፅ እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል።

ባሳለፍነው ቅዳሜ ዕለት በጋቦን ምርጫ ተደርጎ የነበር ሲሆን በምርጫው ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር።

ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮች የተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን ተቆጣጥረዋል።

ወታደራዊ አመራሮች በሀገሪቱ ቴሌቪዥን ባስተላለፉት መልዕክት " የጋቦንን አስተዳደር ይዘናል " ብለዋል።

" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" አስተዳደሩ ኃላፊነት የጎደለውና ወዴት እንደሚሄድ የማይታወቅ ስለሆነ የአገሪቱን ማኅበራዊ ኑሮ በማመሳቀል ወደ ቀውስ ከቶናል " ሲሉም ተናግረዋል።

ወታደሮቹ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ያሸነፉበትን የምርጫውን ውጤት ሰርዘውታል።

በወታደራዊ አመራሮች ከሥልጣን ተወግዷል የተባለው የአሊ ቦንጎ ቤተሰብ ጋቦንን #ለ56_ዓመታት መርቷል ፤ ከነዚህ አመታት ውስጥ አሊ ቦንጎ ብቻቸው 14 ዓመት ሀገሪቱን መርተዋል።

@tikvahethiopia
ጅግጅጋ የሆነው ምንድነው ?

ከሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ እጅግ አሰቃቂ የተባለ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈፅሟል።

የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉ የተፈፀመባት የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ስትሆን ይህ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የድርጊቱ ፈፃሚዎች የደፈሯትን ልጅ ገድለዋታል።

ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት በኃላ ወንጀሉን የፈፀሙ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል።

ነገር ግን ከዚህ የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎችን በመያዙ ሂደት ላይ ሰዎችን ለይቶ በአፈሳ የማሰር ድርጊት እንደነበር ቃላቸውን የሰጡ የጅግጅጋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የጅግጅጋ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፤ ከህፃኗ መደፈር ድርጊት ጋር በተያያዘ ሰኞ 4 ተጠርጣሪዎች ቢያዙም በከተማው ሰፊ አፈሳ ሲደረግ ነበር ብለዋል።

በተለይም ከደቡብ አካባቢ የመጡ ልጆች በድርጊቱ ላይ በመጠርጠራቸው ይህን መሰረት ያደረገ እስር ሲፈፀም እንደነበር ገልጸዋል። ድርጊቱ እስከ ትላንት ድረስ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

አንድ ሌላ ነዋሪ ድርጊቱ እጅግ በጣም አሰቃቂና አስደንጋጭ እንደነበር ገልጸው ከተጠርጣሪዎች አያያዝ ጋር በተያያዘ በፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው ድርጊት ተገቢ አይደለም ብለዋል።

" ተጠርጣሪዎችን በልዩነት ማሰር እየተቻለ ሰዎች በአፈሳ ወደ ማቆያ ሲገቡ ነበር ይህ ተገቢ ያልሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ሌላ አንድ ነዋሪ ደግሞ ፤ " እሁድ እለት አንድ ልጅ ተደፈራ ከተገደለች በኃላ ድርጊቱን የፈፀሙ ግለሰቦች ተይዘው ለህግ ቀርበዋል " ብለዋል።

" ይሄ ጥሩ ነው " ያሉት እኚሁ ነዋሪ ነገር ግን ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የለላቸውን ሰዎች ፓሊስ በጅምላ በማፈስ ማሰረሱን ፣እና መደብደቡን ጠቁመዋል።

በነበረው ሁኔታ የሰዎች ህይወት ማለፉን እንደሰሙ ገልጸዋል።

በተለይ ከደቡብ የመጡ ወጣቶችን መታወቅያ በማየት እስር ፣ ድብደባ ሲፈፀም ነበር ይህን የሚመለከተው አካል ይወቀው ሲሉ ገልጸዋል።

የሶማሌ ክልል መንግሥት ግን ከአሰቃቂው የወንጀል ድርጊት በኃላ ተፈፅሟል የተባለው ድርጊት #አሉባልታ እና #ሀሰተኛ ነው ብሏል።

የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብድቃድር ረሽድ ፤ " በሱማሌ ክልል የሌላ ክልል ተወላጆች እየታፈሡ እየታሰሩ ፣እየተገደሉ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው አሉባልታ ወሬ ነው " ያሉ ሲሆን የሚንገረው ሁሉ ውሸት ነው ብለዋል።

" የሶማሌ ህዝብ ሰፊ ህዝብ ነው አቃፊ ነው ፣ ከየትኛውም ህዝብ ጋር የመኖር ባህል ያለው ማህበረሰብ ነው ፤ የሌላ ኢትዮጵያዊ ተወላጅ የማሳደድ፣ የመግደል ባህል ፈፅሞ የለውም የሚነገረው ሁሉ ውሸት ነው፤ የሶማሌ ህዝብን ስም ለማንቋሸሽ የሚሰራ ፕሮፖጋንዳ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" የህግ አካላት ቦታው ላይ ሳይደርሱ ሁከት ለመፍጠር ሙከራ ተደርጎ ነበር " ያሉት ኃላፊው የህግ አካላት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ የወሰዱት እርምጃዎች ነበሩ ብለዋል።

" እነዛም መቆያ አካባቢዎች ለደህንነታቸው ስጋት የቆዩ አካላት በማጣራት ወደመደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ትላንት በፀጥታ አካላት መመሪያ ተሰጥቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።

" በሶማሌ ክልል ምንም ችግር የለም ሰላም ነው ፤ የሶማሌ ህዝብ አቃፊ ነው " ያሉት ኃላፊው የፖለቲካ አጀንዳ በማድረግ ተቃውሞ በመፍጠር ብጥብጥ ለመፍጠር ፣ በክስተቶች ላይ ክስተት በማጋነን ፣ እከሌ ተገደለ፣ እከሌ ዘሩ እንዲህ ነው በማለት ለፖለቲካ የሚጠቀሙ ኃይሎች አሉ " ብለዋል።

" የሶማሌ ክልል ሰላም ነው ፤ ሁሉም ወደ መደበኛው ስራ ተመልሷል " ሲሉ አክለዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጅግጅጋ የሆነው ምንድነው ? ከሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ እጅግ አሰቃቂ የተባለ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈፅሟል። የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉ የተፈፀመባት የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ስትሆን ይህ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የድርጊቱ ፈፃሚዎች የደፈሯትን ልጅ ገድለዋታል። ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት በኃላ ወንጀሉን የፈፀሙ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል። ነገር ግን ከዚህ የወንጀል ድርጊት…
#ጅግጅጋ

ከሶማሌ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን በተገኘው መረጃ በጅግጅጋ ከተማ የ9 ዓመቷን ልጅ #ደፍረው_ገድለዋል ተብለው የተጠረጠሩት 4 ተጠርጣሪዎች በአባቷ ቤት ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ናቸው።

በልጅቷ አባት ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር ከተባሉት ከአራቱ ተጠርጣሪዎች አንዱ ላይ በዋናነት ምልክቶች እንደሚታዩ የክልሉ መንግሥት አሳውቋል።

ከሚታዩት ምልክቶች አንዱ ፤ ልጅቷን ሲደፍሯት የጥፍሮቿ ምልክት እንዲሁም ደም ይታይበታል ተብሏል።

የወንጀሉ ድርጊት ምርመራ አሁንም እየተካሄደ ሲሆን ክልሉ ምርመራው እንዳለቀ ለህዝብ ይፋ አደርጋለሁ ብሏል።

@tikvahethiopia
በፈጣኑ እና አስተማማኙ የሳፋሪኮም ሜጋ ኢንተርኔት ጥቅል የቤተሰባችንን ጨዋታ እርቀው ላሉ ዘመዶቻችን ያለምንም መቆራረጥ እናጋራ! ወደ *777# በመደወል ዛሬውኑ እንግዛ። ​
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#AAU አንጋፋው የ " #አዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ " በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆነ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው  ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ወስኗል። ውሳኔው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ…
#AAU

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ #የአዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ #ቻንስለር ተደርገው በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተሹመዋል።

ሹመቱ የተሰጣቸው፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ እንዲቋቋም እንዲቋቋም በአዋጅ መጽደቁን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ ከተሾሙት ቻንስለር በተጨማሪ አዳዲስ የቦርድ አመራሮች የተሰየሙለት ሲሆን ፤ ቦርዱም ዩኒቨርሲቲውን በሃላፊነት ሊመሩ የሚችሉ ፕሬዚዳንት እና ም/ፕሬዚዳንቶችን በቀጣይነት እንደሚሾም ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

#Update

ቦርዱ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩን የቦርድ ሊቀመንበር አድርጎ መሾሙን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ደግሞ ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸውን ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#አይቴል

ጥራት ያላቸውን የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች ከሚያቀርቡ ታላላቅ የሞባይል አምራች ኩባያዎች አንዱ የሆነው አይቴል ሞባይል ለኩባንያው አዲስ የሆነውን እና በላቁ ፈጠራዎችን እጅግ ከዘመኑ ግልጋሎቶች ጋር በማጣመር የተመረተውን አይቴል ኤስ23+ ሞዴል በኢትዮጵያ ባዘጋጀው ዝግጅት በይፍ አስተዋውቋል። 

ላለፉት ዓመታት ተወዳጅነት አና ተቀባይነት ያገኙ በአገልግሎት እና በዋጋ ተመራጭ የሆኑ የስልክ ምርቶቹን ለተጠቃሚዎች ሲያቀርብ የቆየው አይቴል ሞባይል  በቴክኖሎጂ እና ዲዛይን ልዩ የሆነውን ብሎም የተለያዩ ግልጋሎቶች በመያዝ የተመረተውን ኤስ23+ አዲስ የሞባይል ሞዴል ማስተዋወቅን ዓላማው ያደረገ ዝግጅት የኩባንያው ሀላፊዎች አና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በታደሙበት ስነስርዓት በይፋ አስመረቀ ።

አይቴል ሞባይል
#ItelMobile #ItelEthiopia #S23+
#CBE

የጋብቻ ቁጠባ ሂሳብ
=========

ጋብቻ ሲያስቡ
የሰርግ ወጪዎን ለመሸፈን፣ ቤትዎን ለማሟላት
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተሻለ ወለድ ጋር በሚሰጠው የጋብቻ ቁጠባ ሂሳብ አገልግሎት አስቀድመው ይቆጥቡ!
***
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• Telegram፡- https://publielectoral.lat/combankethofficial
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጅግጅጋ ከሶማሌ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን በተገኘው መረጃ በጅግጅጋ ከተማ የ9 ዓመቷን ልጅ #ደፍረው_ገድለዋል ተብለው የተጠረጠሩት 4 ተጠርጣሪዎች በአባቷ ቤት ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ናቸው። በልጅቷ አባት ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር ከተባሉት ከአራቱ ተጠርጣሪዎች አንዱ ላይ በዋናነት ምልክቶች እንደሚታዩ የክልሉ መንግሥት አሳውቋል። ከሚታዩት ምልክቶች አንዱ ፤ ልጅቷን ሲደፍሯት የጥፍሮቿ ምልክት እንዲሁም…
#ጅግጅጋ

" እኔ ተጎጂ ነኝ፤ ፍትሕ እፈልጋለሁ " - አባት

በጅግጅጋ ከተማ የተደፈረችው ልጅ አባት ምን አሉ ?

አባት ኡጋስ አረብ በጅግጅጋ ከተማ ወረዳ 13 ተብሎ በሚጠራው ቦታ ልጃቸው በራሳቸው ሰራተኞች ከተደፈረች በኃላ መገደሏን ገልጸዋል።

ለቢቢሲ ሶማሊ ክፍል አባት ኡጋስ አረብ ፦

" እኔ ተጎጂ ነኝ፤ ፍትሕ እፈልጋለሁ። እለኔ ልጅ ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም በዚህ መንገድ ሕይወታቸው ለጠፋ ሁሉ ፍትሕ እንዲሰፍን እጠይቃለሁ።

በወቅቱ መኝታ ቤቴ ውስጥ ተኝቼ ነበር። ቤት ውስጥም ከእኔ ውጭ ትልልቅ ሰዎች አልነበሩም።

ልጄ ጋር ሄጄ ሳያት እየተነፈሰች አልነበረም ደረቷንም በመጫን እንድትተነፍስ ለማድረግ ሞከርኩ።

አንገቷንም ሳየው ገመድ ተጠምጥሞባት ታንቃለች። ገመዱን ቆርጬ ወደ ሐኪም ወሰድኳት።

ለሕክምና ወደ ሆስፒታል አፋፍሰን ብንወስዳትም ሕይወቷ አልፏል።

በሞባይል ጥገና ሱቄ ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ አራቱ ሠራተኞቼ በድርጊቱ ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል። አንደኛው ሠራተኛዬ ጠፍቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።

Via BBC Somali

@tikvahethiopia