TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"አቶ በረከት #ለፍርድ መቅረብ አለበት"፡ አና ጎሜዝ - BBC⬇️

📌ጥያቄ፡- ሰሞኑን አቶ በረከትን ቃለ መጠይቅ አድርገንላቸው ነበር። 'ወ/ሮ አና፣ 'እባክዎ አርፈው ይቀመጡ' ብለዎታል፡፡ እንዲያውም እኚህ ሴትዮ ‹‹የፖርቹጋል #ቅኝ ግዛት #አስተሳስብ አልለቀቃቸውም››፤ ሲሉ ነው አስተያየት የሰጡት።

▪️ወይዘሮ አና ጎሜዝ፡- ለእንዲህ ዓይነት የወረደ ሐሳብ መልስ መስጠት አልሻም ነበር። አገሬን መስደባቸው ግን ትክክል አይደለም። እኔን እና አገሬን ከቅኝ ግዛት ጋር ማያያዛቸውም #አሳፋሪ ነው። በፖርቹጋል እኔ የምታወቀው በጸረ ቅኝ አገዛዝ ተጋድሎዬ ነው። ያውም ቅኝ ግዛትን መጻረር ፈታኝ በሆነበት ዘመን ነው የምልህ። ሕይወቴንም አደጋ ላይ ጥዬ ነው ይሄን ያደረገኩት። ተማሪ እያለሁ ጀምሮ ነው ይሄን ተጋድሎ የፈጸምኩት። ታሪኬ የሚያስረዳውም ይህንን ነው።

📌ጥያቄ፡- ሁለታችሁን እንዲህ የቃላት ጦርነት ውስጥ የሚከታችሁ እኛ የማናውቀው ነገር አለ?

▪️አና ጎሜዝ፡- ነገሩ በ2005 እኔ የአውሮፓ ምርጫ ታዛቢ ቡድንን መምራት በጀመርኩበት ጊዜ የሆነ ነው። እሱ ያኔ የመንግሥት ተወካይ ነበር። ከእኔና እኔ ከምመራው የምርጫ ታዛቢ ቡድን ጋር እሱ ነበር በየጊዜው የሚገናኘው። የፕሮፓጋንዳ ሚኒስትርም ነበር። በዚያ የታዛቢ ቡድን አማካኝነት እኔና የቡድኔ አባላት የተደረገውን ማጭበርበር ስላጋለጥን ነው በእኔ ላይ ቂም ይዞ የቆየው። ከበረከት ስምኦን ጋር በጁን 8፣ 2005 የነበረንን ንግግር መቼም አልረሳውም። በመሐል አዲስ አበባ የተደረገውን ግድያ ሰምቼና ሆስፒታሎችን ጎብኝቼ ወዲያውኑ አገኘሁት። የጎበኘኋቸው ሐኪሞችና ነርሶች እያለቀሱ ነበር [በጥይት የተመቱትን] የሚያክሙት፡፡ ሁኔታው አስቆጥቷቸው ነበር። ባየሁት ጉዳይ ላይ መግለጫ እንደምሰጥ በረከትን ነገርኩት። እርሱ በዚህ ውሳኔዬ ተበሳጨ፡፡ ይባስ ብሎ
ለተፈጠረው ግድያ ተጠያቂው የአውሮፓ ኅብረት ነው አለኝ። ይህ ብሽቅ የኾነ ሐሳብ ነው።

📌ጥያቄ፡- በቀደም ለታ የትዊተር ገጽዎ አቶ በረከትን ‹‹ርህራሔ የሌለው፣ ዋሾና፣ ጨካኝ›› ብለውታል። አልበዛም? የተጠቀሟቸው ቃላቶች የዲፕሎማት ቋንቋ አይመስልም።

▪️አና ጎሜዝ፦ #እውነት ስለሆነ ነዋ፣ እውነት ስለሆነ ነው፥ እርሱ ጨካኝና #ውሸታም ነው። በ2005 በደንብ አውቀዋለሁ ሰውዬውን። ባህሪው እንደዚያ ነው። እኔ ከአገሪቱ ጋር ምንም ችግር የለብኝም። የኔ ችግር ሁልጊዜም ከአምባገነኖች ጋር ነው።

📌ጥያቄ፡- አሁን ነገሩ ረዥም ጊዜ ሆነው እኮ፤ ለምን አይረሱትም ግን እርስዎ?

▪️አና ጎሜዝ፡ - ለምን እረሳለሁ?! በ2005ቱ ምርጫ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ሞተዋል። የነርሱ ቤተሰቦች ይህን የሚረሱ ይመስልኻል? ስለዚህ እኔም አልረሳም። የሰው ሕይወት ነው የጠፋው፤ ለግድያው ኃላፊነት መውሰድ ያለባቸው ሰዎች አሉ፤ አንዱ አቶ በረከት ነው። ይህን ጉዳይ የግለሰቦች ጉዳይ ለምን ታደርገዋለህ። እኔ በግል ከሰውየው ጋር ምንም ችግር የለብኝም እኮ። ፖለቲካዊ ነው ጉዳዩ። በርካታ ሰዎችን የጨፈጨፈውን ሥርዓት ሲያገለግል የነበረ ሰው ነው። እኔ ለማወቀውና ለፈጸመው ወንጀል ተጠያቂ ይሁን ነው እያልኩ ያለሁት። ብቸኛው ተጠያቂ እንዳልሆነ አውቃለሁ። ሆኖም አንዱና ዋንኛው ነው።

📌ጥያቄ፡- ለማለት የፈለኩት ከእርስዎ ጋር ምርጫውን የታዘቡ፣ የኾነውን የተመለከቱ ብዙ ዲፕሎማቶች ነበሩ፤ አንዳቸውም በእርስዎ መጠን መንግሥት ላይ ትችት ሲሰነዝሩ አልሰማንም። እርስዎ ለምንድነው አንዲህ ነገሩን ለዓመታት የሙጥኝ ያሉት?

▪️አና ጎሜዝ፡ - ዲፕሎማቶች የተፈጠሩት እንዲዋሹ አይመስለኝም። ዝም አልልም፤ ለምን ዝም እላለሁ፤ በመለስና በአቶ በረከት ትእዛዝ የተገደሉ ሰዎችን አይቻለሁ፤ #ስለምን ዝም እላለሁ? አሁንም ላረጋግጥልህ የምፈልገው፤ አሁንም ወደፊትም ዝም አልልም። ሌሎች ዝም ብለዋል ላልከው እኔ ያኔም ያስተጋባሁት የ200 የቡድኔን አባላት በመላው ኢትዮጵያ ተዘዋውረው ያዩትን ነው። ያወጣነው ሪፖርት ደግሞ ከካርተር ሴንተር ካወጣው ሪፖርት ጋር የሚመሳሰል ነው። ነገር ግን ሁሉም ሰው ለአንድ ጉዳይ የሚሰጠው ምላሽ ተመሳሳይ ላይሆን ይችላል። እኔ ባየሁት ነገር እጅግ ተቆጥቻለሁ። የመለስና የበረከት መንግሥት የሕዝብን ድምጽ ያጭበረበረበት መንገድ አናዶኛል። የአውሮፓ አገራት ይህንን መንግሥት እሹሩሩ ያሉበት መንገድ አበሳጭቶኛል። አሁንም ዝም አልልም፤ ወደፊትም ዝም አልልም፤ በእጃቸው የሰው ደም ያለባቸውን እንደ አቶ በረከት ያሉ ሰዎችን በዝምታ አላልፋቸውም።

📌ጥያቄ፡- አቶ በረከት ወንጀለኛ ናቸው ለፍርድ ይቅረቡ እያሉ ነው?

▪️አና ጎሜዝ፡- ይሄ ምን ጥያቄ አለው፤ አቶ በረከት ለፍርድ ነው መቅረብ ያለበት። እርግጥ ነው ብቻውን አይደለም፤ ግን ዋናው ሰው ነው፤ ለፍርድ የማይቀርበው ለምንድነው? አሁን ለውጥ ላይ ያለው መንግሥት ወደዚህ ድምዳሜ ላይ ይመጣል የሚል ተስፋ አለኝ።

📌ጥያቄ፡- የአቶ በረከት ስምኦንን ጉዳይ ለጊዜው ገሸሽ እናድርገውና፤ ሌላ ጥያቄ ላንሳ፤ በ2012 አቶ መለስ ዜናዊ በብራስልስ መሞታቸውን #ለኢሳት መረጃ ያቀበሉት እርስዎ ኖት እንዴ?

▪️አና ጎሜዝ፡- ሊሆን ይችላል። መረጃው ነበረኝ። ያኔ ማንም መለስ ዜናዊ መታመሙን ቀርቶ አገር ውስጥ አለመኖሩንም የሚያውቅ ብዙ ሰው
አልነበረም። #መሞቱንም ብዙ ሰው አያውቅም ነበር። የነበረኝ መረጃ እጅግ #አስተማማኝ የሚባል ነበር። ያን መረጃ ኢሳት የተጠቀመበት ይመስለኛል። ቀደም ብሎ መሞቱን የነገረኝ ምንጭ እጅግ የምተማመንበትና አስተማማኝ ነበር።

📌ጥያቄ፡- ስለዚህ አቶ #መለስ የሞቱት በመንግሥት #ከተገለጸው ቀን ቀደም ብሎ ነው ብለው በእርግጠኝነት መናገር ይችላሉ?

▪️አና ጎሜዝ፡- ያለምንም ጥርጥር። መጀመርያ ብራዚል ለሕክምና ተወስዶ ነበር። ከሐኪሞቹ ጋር በብራዚል ተገናኝቷል። የሕመሙ ሁኔታ
የተገመገመው ብራዚል በሚገኙ ስፔሻሊስቶች ነበር። ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ተነገረው። ከዚያ በኋላ ነው ብራስልስ እንዲመጣ የተደረገው። እኔ መረጃውን ባገኘሁበት ቅጽበት ራሱ ከቀናት በፊት መሞቱ ነው የተነገረኝ። ሆኖም በምሥጢር ተይዞ ነበር።

📌ጥያቄ፡- ትክክለኛ ቀኑን ያስታውሱታል?

▪️አና ጎሜዝ፡- አላስታውስም

📌ጥያቄ፡- የትኛው በሽታ ለሞት እንደዳረጋቸውስ ያስታውሳሉ?

▪️አና ጎሜዝ፡- እ…አንዳች የካንሰር ዓይነት ሕመም ሳይሆን አይቀርም፤ በትክክል ምን እንደነበር እርግጠኛ አይደለሁም።

📌ጥያቄ፡- መንግሥት ለምን መሞታቸውን ዘለግ ላለ ጊዜ መደበቅ የፈለገ ይመስልዎታል?

▪️አና ጎሜዝ፡- እነርሱን ነው መጠየቅ ያለብህ። ነገር ግን በአምባገነን መንግሥታት ውስጥ የጠንካራ መሪ ሞት መደበቅ የተለመደ ነው፤ #የመለስን ሞት #ቀደም ብዬ አውቅ ነበር እያልኩህ አይደለም። እንደሰማሁት መረጃውን ሰጠሁ። ብዙም ሳይቆይ መንግሥትም መሞታቸውን አረጋገጠ። ከዚያ በፊት ግን ስለመታመማቸው እንኳን ለኢትዯጵያ ሕዝብ አልተነገረም ነበር።

📌ጥያቄ፡- እርስዎ መች ነው ግን ለመጀመርያ ጊዜ ኢትዮጵያ የሚለውን ስም የሰሙት?

▪️አና ጎሜዝ፡- በልጅነቴ ነው። በቅኝ ግዛትና ከቅኝ ግዛትም በፊት በነበረው የአገሬ ታሪክ ወስጥ የኢትዮጵያ ስም ገናና ነው። ፖርቹጋሎች ለረዥም ዓመት ኢትዮጵያ በእግር ተጉዘው ለመድረስ ይሞክሩ ነበር። የፕሪስት ጆን አገር ተብላ ትታወቅ ነበር። የፖርቹጋል አሳሾች ትልቅ ጉጉት ነበራቸው፤ ይቺን አገር ለማየት። እኔ አገሪቱን የረገጥኩት በ97 ምርጫ ጊዜ ነው።
.
.
ይቀጥላል🔄
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር ዐብይ ድሬዳዋ ለምን ቀሩ??

ከሳምንታት በፊት ጠ/ሚር #አብይ_አህመድ በድሬዳዋ የልማት ፕሮጀክቶችን ለመመረቅ አስበው በመጨረሻ ሰአት ጉዟቸውን #የሰረዙበት ምክንያት ከፀጥታ ችግር ጋር የተያያዘ መሆኑን የከተማዋ ሁለት ሀላፊዎች በተለይ ለEthio NewsFlash ገልፀዋል። አንዱ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ሀላፊ እንዳመለከተው ወደ ፕሮጀክቶቹ ከሚወስዱት መንገዶች አንዱ የመልካ መንገድ ዙርያ #የጦር_መሳርያ በብዛት በወቅቱ #እንደተገኘ ሲገልፅ ሁለተኛው ሀላፊ ደግሞ ሌሎች የመንገድ አማራጮችን ጠ/ሚሩ ተጠቅመው መሄድ ቢችሉም የፀጥታው ሁኔታ #አስተማማኝ ስላልነበር ሙሉ ለሙሉ ጉዞው ተሰርዟል ብለዋል። ነገር ግን ሁለቱም ሀላፊዎች ጠ/ሚሩ በወቅቱ ኢላማ ውስጥ እንደነበሩ ተጠይቀው በግልፅ ከመናገር ተቆጥበዋል።

via ETHIO NEWSFLASH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መከላከያ‼️

ድሬዳዋን ሰላምና ፀጥታ #አስተማማኝ በማድረግ የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንዲፈቱ እንደሚሰራ #በምስራቅ_ዕዝ_መከላከያ የሚመራው ጊዜያዊ የፀጥታ ጥምር ኮሚቴ አስታወቀ።

ኮሚቴው ምሽት ላይ በሰጠው #መግለጫ #በመልካ_ጀብዱ የሞቱት ሁለት ሰዎች ሰሞኑን ከተከሰተው የወጣቶች  ተቃውሞና ሰልፍ ጋር አይገናኝም፡፡

ጊዜያዊው የፀጥታ ጥምር ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ ሰሞኑን ሁከትና ተቃውሞ የተነሳባቸው አካባቢዎች ሰላምና ፀጥታ ሰፍኖ ማህበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ እንቅስቃሴዎች እንደወትሮው እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡

ኮሚቴው ገለልተኛ ሆኖ የህግ የበላይነት ማረጋገጥና የህዝብ ሰላምና ደህንነት የመጠበቁን ተግባራት በቋሚ ስፍራዎች ሰራዊት በመመደብና  በተንቀሳቃሽ መኪኖች በመታገዝ እያከናወነ ይገኛል፡፡

የጥምር ኮሚቴው አባልና የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌታቸው አስረስ “በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ሁለት መቶ ተጠርጣሪዎች መካከል ከጉዳዩ ጋር የማይገናኙት እየተለቀቁ ናቸው” ብለዋል።

ሌሎቹን መርማሪዎች ቃል እየተቀበሉ ይገኛሉ፤መረጃና ማስረጃ እየተሰባሰበባቸው በመሆኑ ይህ እንደተጠናቀቀ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ብለዋል፤ ታዳጊ ወጣቶች ተገቢው ምክርና ትምህርት ተሰቷቸው መለቀቃቸውንም ተናግረዋል።

ጂቲ ዜድ በተባለ ስፍራ በተካሄደው ሁከትና ብጥብጥ ሶስት ሸጉጥና ሁለት ክላሽንኮቭ ጠመንጃ መያዙን ተናግረዋል።

የጥምር ኮሚቴው አባል የፌደራል ፖሊስ የምስራቅ ክላስተር ኃላፊ ኮማንደር ሰለሞን ከበደ በበኩላቸው “ትላንት በመልካ ቀበሌ የተከሰተው ግጭት አስቀድሞም ለዓመታት የዘለቀና በአካባቢው ነዋሪዎች መካከል ሲፈጠር የነበረ እንጂ ከሰሞኑ ችግር ጋር አይገናኝም” ብለዋል፡፡

በግጭቱ ወደ አዲሱ ምድር ባቡር ሰው ሊያደርስ ሲጓዝ የነበረ ወጣት የታክሲ ሹፌርና አንድ ሌላ ሰው መሞታቸውን ተናግረዋል፡፡

ወንጀሉን የፈጸሙ አምስት ሰዎች በህግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውንም ገልፀው ሌሎቹንም በቁጥጥር ሥር የማዋል ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡

የፀጥታ አካሉ በድሬዳዋ አስተማማኝ ሰላም ለማምጣት የጀመረው ሥራ ስኬታማ እንዲሆን ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ማድረግ እንዳለበት የተናገሩት ደግሞ የኮሚቴው አባል የድሬዳዋ ፍትህ ፀጥታና የህግ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ ናቸው፡፡

ችግሩ ከኃይማኖትና ከብሔር ግጭት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌለው አስረድተው ለዚህም ሌት ተቀን የሚሰሩ አካላት መኖራቸውን በመገንዘብ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ ከሰፈነ በኋላ የፖለቲካ አመራሩ የወጣቱን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የመፍታት ስራ ያከናውናል” ብለዋል፡፡

የጥምር ኮሚቴው ሰብሳቢ የምስራቅ ዕዝ የኢንዶክትሬሽንና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮሎኔል ፍስሃ ተክለሃይማኖት በበኩላቸው ፀጥታው አስተማማኝ ደረጃ እስኪደርስ ሰራዊቱ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት  እያከናወነ የሚገኘውን ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 19/2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባው ስካይ ላይት ሆቴል ዛሬ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት በይፋ ተመርቆ ተከፍቷል፡፡
.
.
#ሐሰተኛ_የማስተርስና_የዶክትሬት ዲግሪዎች እንዲሰጡ አድርገዋል የተባሉት የሜቴክ ኃላፊዎች ላይ ክስ ተመስርቷል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ #የድሬዳዋ ተወላጆች በዛሬው ዕለት በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተገኝተው ያላቸው ተቃውሞ እና ቅሬታ አሰምተዋል። የፌደራሉ መንግስት ለድሬዳዋ ከተማ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥና ያሉ ችግሮችን እንዲፈታ ጠይቀዋል።
.
.
#የሰላሌ_ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትናንት ቅዳሜ "አንድ ቀን ለማህበረሰቤ" በሚል መሪ ሀሳብ #ፍቼ ከተማን ሲያፀዱ ውለዋል።
.
.
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን ቆላማ አካባቢ የስንዴ ግብርና ልማት የሙከራ ፕሮጀክትን ጎብኝተዋል።
.
.

4ኛው የኢህአዴግ የወጣቶች ሊግ ድርጅታዊ ጉባዔ #በሃዋሳ_ከተማ ዛሬ ተጀምሯል። ጉባዔው "በተጠናከረ የወጣቶች ትግል ሀገራዊ ለውጡን ወደፊት" በሚል መሪ ቃል እስከ ጥር 19 እስከ 21 በተለያዩ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እየመከረ ይቆያል፡፡
.
.
በቤኒሻንጉል ጉሙዝና ኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን አጎራባች ወረዳዎች በተከሰተው #ግጭት ምክንያት የተፈናቀሉ ወገኖች መልሶ በሚቋቋሙበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።
.
.
በጅማ ከተማ "ንግዳችንን እናዘምን" በሚል መሪ ቃል የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በዛሬ ዕለት ተካሂዷል።
.
.
ትውልደ ኢትዮጵያዊው ቢሊየነር ሼህ መሃመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ከእስር መፈታታቸው ተሰምቷል።
.
.
የቀድሞ ጦር ማህበር #የምስረታ_ጉባዔ ዛሬ #በደብረማርቆስ ፖሊስ ኮሌጅ ተካሂዷል።
.
.
ለአራት ቀናት በመቀለ ሲካሄድ የቆየው የትግራይ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት የአምስተኛው ዘመን 14ኛው መደበኛ ጉባኤ አዋጆችንና ሹመቶችን በማጽደቅ #ተጠናቋል
.
.
የድሬዳዋን ሰላምና ፀጥታ #አስተማማኝ በማድረግ የህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንዲፈቱ እንደሚሰራ #በምስራቅ_ዕዝ_መከላከያ የሚመራው ጊዜያዊ የፀጥታ ጥምር ኮሚቴ አስታውቋል።
.
.
ምንጭ፦ ኢዜአ፣ DW፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ የጠ/ሚ ፅ/ቤት፣ የምክትል ጠ/ሚ ፅ/ቤት፣ etv፣ ዋልታ፣ ፋና፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
የነገ ሰው ይበለን!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ‼️

የመልካም አስተዳደርና የሥራ  አጥነት መሠረታዊ ጥያቄዎች በፍጥነት ለመመለስ የሚያግዝ የ60 ቀናት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ተናገሩ።

የድሬዳዋ አስተዳደርና የሐረሪ ክልል ፖሊስ ገለልተኛ ሆኖ አገር አቀፍ ለውጡን በሚያግዝ መንገድ ማዋቀር /ሪፎርም/ እንደሚያስፈልግ የፀጥታ ጊዜያዊ ኮሚቴ ሰብሳቢ ብርጋዲዬር ጄኔራል #ተስፋዬ_ወልደማርያም አስታውቀዋል፡፡

ዕቅዱ ሕዝብ #ብሶቱን የሚያሰማባቸውን 17 መሠረታዊ ጉዳዮች በመለየት  ሁሉን አቀፍ ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቱን ከንቲባው አቶ #ኢብራሂም_ዑስማን አስታውቀዋል፡፡

አመራሩ ከፖለቲካ ፣ከሰላምና ፀጥታ እንዲሁም ከልማትና ከመልካም አስተዳደር አኳያ የተጀመረውን እንቅስቃሴ ዳር ለማድረስ  መሥራት እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡

”በዕቅዱ መሰረት የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ጭምር በማጠናቀቅ የሕዝቡን  የዓመታት ጥያቄ ምላሽ የሚያገኝበት ይሆናል። በየሥፍራው የተገነቡ የመሸጫና የማምረቻ ቦታዎች ለወጣቱ ይሰጣሉ” ብለዋል፡፡

ከሚመለከተው የበላይ አካል ጋር በመነጋገር ፖሊስ በአስቸኳይ ወደ ሪፎርም እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡

ኅብረተሰቡ ዕቅዱ ስኬታማ ለማድረግ ድጋፍና ትብብር ከማድረግ ጎን ለሰላምና #ለፀጥታ መረጋገጥ ግንባር ቀደም ኃላፊነቱን እንዲወጣ ከንቲባው ጠይቀዋል፡፡

የድሬዳዋ ጊዜያዊ የፀጥታ ኮሚቴ ሰብሳቢ የምሥራቅ ዕዝ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽን ብርጋዲዬር ጄኔራል ተስፋዬ ወልደማርያም በከተማዋ ሰሞኑን የተፈጠረው ሕገ-ወጥ ተግባራትና ሁከት መንስዔ አመራሩ የተሰጠውን ኃላፊነት ባለመወጣቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሁንም አመራሩ ባለበት ተጠያቂነትና ይቅርታ በመጠየቅ ዕቅዱን በማከናወን ሕዝቡን መካስ እንዳለበት አሳስበዋል። ”ሕዝቡን የማያገለግል አመራር መነሳት አለበት፤ በብጥብጥና ሁከት ውስጥ የተገኘ አመራር የማያስፈልግና በሕግ መጠየቅ ያለበት ይሆናል” ብለዋል፡፡

ኅብረተሰቡ ለውጥ በሂደት የሚመጣ  መሆኑን በመገንዘብ አገራዊ ለውጡን ለማደናቀፍና በሚፈለገው መንገድ አንዳይጓዝ የሚፈልጉ አካላትን በተቀናጀ መንገድ መከላከል እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

ብርጋዲዬር ጄኔራል ተስፋዬ እንደተናገሩት በድሬዳዋም ሆነ በምሥራቁ የአገሪቱ ክፍል #አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ የሚያሰፍን ዕቅድ ተዘጋጅቶ  በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡

ሰሞኑን በድሬዳዋ በተፈጠረው ሁከትና ነውጥ በማራገብ ሂደት #ፖሊስና #አድማ_በታኝ አሉበት፤ ይህም በፖሊስ ውስጥ መሠረታዊ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ያመለክታል ብለዋል።

በመሆኑም የድሬዳዋ አስተዳደርም ሆነ የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽኖች ውስጥ ሥር ነቀል ለውጥ ማድረግና የኅብረተሰቡን ሰላምና ፀጥታ በአስተማማኝ መንገድ መጠበቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ምንጭ፦ ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአማራ ክልል #የተሻለ እና #አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ሕጋዊ ትጥቅን ‹‹የማስፈታት ሥራ እንደተጀመረ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ከእዉነት የራቀ ነዉ›› ተብሏል፡፡ ተጨማሪውን ያንብቡ👇

https://telegra.ph/አማራ-ክልል-ETHIOPIA-07-04
TIKVAH-ETHIOPIA
#አቶ_ርስቱ_ይርዳው ቀጣዩ የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንት ማን ይሆኑ? TIKVAH-ETHIOPIA ከቤተሰቡ አባላት ታማኝ ምንጮች እንደሰማው ከሆነ-አቶ ሚሊዮን ማቲዮስን በመተካት የደቡብ ክልልን በፕሬዘዳንትነት የሚመሩት አቶ #ርስቱ_ይርዳው ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። •በትላንትናው ዕለት #ሪፖርተር_ጋዜጣ የደቡብ ክልል ቀጣይ ፕሬዘዳንት አቶ መለስ አለሙ ሆነው ሊሾሙ እንደሚችሉ መግለጹ አይዘነጋም። @tsegabwolde…
ፎቶ📸አቶ ርስቱ ይርዳው🤝አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ👆

የደቡብ ክልል ምክር ቤት አቶ ርስቱ ይርዳውን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አድርጎ #ሾሟቸዋል። ትላንት ምሽት የTIKVAH-ETHIOPIA ቤተሰብ አባላት የሆኑ ታማኝ ምንጮች የአቶ #ርስቱ_ይርዳውን ሹመት በሚመለከት #አስተማማኝ መረጃ አካፍለውን እንደነበር ይታወሳል።

#TIKVAH_ETHIOPIA_FAMILY

ፎቶ: የደቡብ ክልል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

እስካሁን ድረስ #አስተማማኝ የሆነና #ዘላቂ መፍትሄ ያልተገኘለት የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ዳግም ሌላ የከፋ እልቂት እንዳያስከትል ከፍተኛ ስጋትን ደቅኗል።

ከጥቂት ወራት በፊት ተደርሶ የነበረው ለሰብዓዊነት ግጭት የማቆም ውሳኔ መላ ህዝብ በተስፋ ሲጠብቅ የነበረውን ጥቂት የሰላም ጭላንጭል አሁን እየታየ ያለው የዳግም ጦርነትና ግጭት ሁኔታ የታየውን ተስፋ እንዳያጨልመው ስጋት ደቅኗል።

በእርግጥ ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ ተብሎ በታወጀበት ወቅት እንኳን በየአቅጣጫው ያሉትና ለዚህ ወገን እንወግናለን የሚሉ ሚዲያዎች ፣ አክቲቪስቶች፣ ፖለቲከኞች የጦርነት እና ግጭት ቅስቀሳዎች፣ ጥላቻንና የሰዎችን አእምሮ ለዳግም ጦርነት የማዘጋጀት ድርጊትና እቅስቀሳ አላቆሙም ነበር።

እስካሁን ባለው ጊዜ አቀራራቢ እና ሰላም ላይ ትኩረት ያደረጉ ስራዎች በአግባቡ አልተሰሩም ፤ ግጭት ቆመ ይባል እንጂ በተለይ በሚዲያ የሚሰራው ስራ ሰዎች ከጦርነት ስነልቦና እንዳይወጡ የሚያደርግ ነበር።

በተለያዩ አካላት እየተሞከሩ ነው ስለሚባሉት የሰላም ጥረቶች መላው ህዝብ ይሄ ነው የሚባል ዝርዝር መረጃ የለውም ፤ ይህንን ጥረት የሚያደርጉ አካላትም ለስራው እንቅፋት እንዳይሆነ መረጃውን ለመስጠት ባለመፈለጋቸው ከኃላ ለሰላም እና ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት ስለሚደረገው ጥረት እና እንቅፋት ስለሆኑ ጉዳዮች በትክክል ማወቅም አልተቻለም።

ከሰሞኑ ግን ከፍተኛ የጦርነት ዝግጅቶችና ቅስቀሳዎች ፣ የሚዲያ ዘመቻዎች ከየአቅጣጫው ተጧጡፈው በመቀጠለቸው ለሰላም የነበረውን ተስፋ ዳግም እያደበዘዘው ይገኛል።

ሌላው በትግራይ ክልል ላለው በብዙ ሚሊዮን እርዳታ ጠባቂ ግጭት የማቆም ውሳኔ ከተደረሰ በኃላ በየቀኑ መግባት የነበረበት 100 ተሽከርካሪ ለምን እየገባ እንዳልሆነ ለዚህ ደግሞ ማን ? ምን ? እንቅፋት እንደሆነ በግልፅ የሚያብራራ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ አድራጊ ድርጅትም ብቅ አላለም።

የሆነው ሆኖ ግን አሁን ላይ በየአቅጣጫው የሚታየው የግጭት እና የጦርነት ቅስቀሳ ፣ ጥላቻን የመዝራት ዘመቻ ዳግም የከፋ እልቂት እንዳይመጣ የሚያሰጋ ሲሆን፤ ከግጭት እና ጦርነት ቀጠና ራቅ ያሉ አካላት ገና ከወዲሁ በሁኔታው የዩትዩብ ገንዘብ መሰብሰቢያ ፣ የፖለቲካ ትርፍ ማግኛ ማድረግ ጀምረዋል።

ከዚህ በፊት በነበረ ጦርነት ሳቢያ እጅግ የተዳከመው ኢኮኖሚ፤ አሁን በሩስያና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት በዓለም ያለው ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚያዊ መናጋት በሀገር ውስጥ ዳግም ጦርነት ተደርጎ ኢኮኖሚው እንዳያንሰራራ ሆኖ እንዳይወድቅ ያስፈራል ፤ ይህ ደግሞ ይዞት የሚመጣው መዘዝ እጅግ የከፋ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Oromia " የልዩ ኃይል ስምሪት አቁመናል ፤ ... በክልሉ ያለውን የፀጥታ ማስከበር ሥራ የአገር መከላከያ ሠራዊት ተረክቧል " - የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የልዩ ኃይል አደረጃጀት ስምሪት ማቆሙን አስታወቀ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ ነው ይህንን ያሳውቁት። ዋና ኮሚሽነሩ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ፤  የፌዴራሉ…
#Oromia

የክልል ልዩ ኃይሎችን መልሶ የማደራጀት ተግባር መጀመሩን ተከትሎ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የልዩ ኃይል ስምሪት #ማቆሙን ገልጿል።

በክልሉ ያለውን የፀጥታ ማስከበር ስራ የአገር መከላከያ ሰራዊት መረከቡንም አሳውቋል።

የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ጄነራል አራርሳ መርዳሳ ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ ነው ይህን ያሉህ።

ኦሮሚያ የሚንቀሳቀሰው መንግሥት " ሸኔ " እያለ የሚጠራውና እራሱን የኦሮሞ ነጻነት ጦር ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን የመንግሥትን ጥሪ በመቀበል እንቅስቃሴውን የሚያቆም ከሆነ በክልል ሌሎች የፀጥታ ሥራዎች #በመደበኛ_ፖሊስ እንደሚከወኑ ያሳወቁት ጄነራል አራርሳ ለጊዜው ግን የዜጎች ደህንነት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ የመከላከያ መከላከያ ሰራዊት ኃላፊነቱን ተረክቧል ብለዋል።

በኦሮሚያ ላይ አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታው #አስተማማኝ_እንዳልሆነ ያልሸሸጉት ኮሚሽነሩ በተለያየ ስያሜ በመንቀሳቀስ ኅብረተሰቡን የሚያፈናቅሉ መኖራቸውን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃለምልልስ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
#CBE

ኢትዮ-ዳይሬክት (EthioDirect)

• በሞባይል ስልክዎ
• የቪዛ እና ማስተር ካርድዎን በመጠቀም
• ያለምንም ክፍያ
• ከውጭ ሀገራት 
• ወደ ሀገር ውስጥ 
• ቀጥታ ወደተቀባዩ ሂሳብ 
• ገንዘብ የሚልኩበት የሞባይል መተግበሪያ!

#ቀላል #ፈጣን #አስተማማኝ #ነፃ 
=============
የEthioDirect  መተግበሪያን ከPlay Store ወይም ከApp Store በማውረድ የአግልግሎቱ ተጠቃሚ ይሁኑ!

•  ለአንድሮይድ ስልኮች፡- https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
•  ለአይፎን ስልኮች፡- https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491