TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia ከጥቂት ቀናት በፊት አገልግሎታቸው እንዲገደብ የተደረጉት የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ዛሬም አገልግሎታቸው ወደ ቦታው እንዳልተመለሰ ለመረዳት ታችሏል። #ቴሌግራም ጨምሮ ሌሎች የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች አገልግሎታቸው እንዲገደብ ከተደረገ ቀናት ያለፉ ሲሆን ጉዳዩን በተመለከተ ያብራራ/ያሳወቀ የለም። የአገልግሎት ገደቡ በሁለቱም የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎች (ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም…
#ETHIOPIA

በኢትዮጵያ የማህበራዊ መገናኛዎች ላይ ገደብ ከተገደረገባቸው ስድስተኛ ቀኑን ይዟል።

" #ቴሌግራም " ን ጨምሮ ሌሎች የማህበራዊ መገናኛዎች ምክንያቱ በግልፅ ወይም በይፋ ባልተነገረበት ሁኔታ ገደብ ከተደረገባቸው ስድስተኛ ቀን ሆኗል።

ይህ መልዕክት ተፅፎ እስከተላከበት ሰዓት ድረስ አገልግሎቶቹ ያልተመለሱ ሲሆን በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉት ሁለቱም የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎች " ኢትዮ ቴሌኮም " እና " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ " አማካኝነት አገልግሎት ማግኘት አልተቻለም።

የአገልግሎት ገደብን በተመለከተ " በዚህ ምክንያት ነው ፤ ለዚህን ያህል ጊዜም ይቆያል " ብሎ ያብራራ አካል እስካሁን ብቅ አላለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ቤተሰቦቹ ለማጣራት ባደረገው ጥረት በሁለቱም የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎች " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ኢትዮ ቴሌኮም "  ቴሌግራም፣ ፌስቡክ፣ ቲክቶክ ፣ ዩትዩብ የመሳሰሉት የማህበራዊ መገናኛዎች አገልግሎት እየሰጡ የማይገኙ ሲሆን #ትዊተር፣  #ኢንስታግራም እና #ዋትስአፕ ገደብ ሳይደረግባቸው አገልግሎት እየሰጡ ነው።

ምንም እንኳን በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ አገልግሎቶች ላይ ገደብ ተጥሎ ቢገኝም በVPN አገልግሎቱን ማስቀጠል ይቻላል፤ ከዚህ ቀደም መሰል እርምጃዎች ከተወሰዱበት ጊዜ አንፃር ሲታይ በዚህኛው ከፍተኛ የሰው ቁጥር አገልግሎት ለማግኘት VPN የመጠቀም ሁኔታው መጨመሩን ከቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ለመረዳት ችለናል።

@tikvahethiopia