TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ባህርዳር

በባሕር ዳር ከተማ 19 ሽጉጥ እና 1 ክላሽንኮቭ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ተደብቀው ከተያዙት19 ሽጉጥና 1 ክላሽንኮቭ በተጨማሪ 3 ሺህ 427 መሰል ጥይቶችም ተይዘዋል። ህገ ወጥ የጦር መሳሪያው በቁጥጥር ስር የዋለው በአንድ ግለስብ ውስጥ መሳሪያው እንዳለ በደረሰ ጥቆማ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡ ግለሰቡ በባህር ዳር ጣና ክፍለ ከተማ ተከረይቶ የሚኖር እንደሆነም የአማራ መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ዘግቧል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባህርዳር

በኢትጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በህገ ወጦች ሲንቀሳቀስ የነበረ ንብረትን በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስታውቋል፡፡የተለያዩ አልባሳት እና ህገ ወጥ የአሳ ማስገሪያ መረቦች ናቸው በፖሊስ የተያዙት፡፡ በሁለት አይሱዙ መኪናዎች ተጭነው ከሁመራ ወደ ጎንደር ከተማ ሊገቡ እያለ ትክል ድንጋይ ላይ እንደተያዙ ጽህፈት ቤቱ ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ዛሬ በላከው መረጃ አስታውቋል፡፡

የንብረቶቹ ግምታዊ ዋጋ ከ 2 ሚሊዮን 170 ሺህ ብር በላይ እደሚሆንም ነው የተገለጸው፡፡ ንብረቶቹን የያዙት የአማራ ክልል ፖሊስ አባላት ናቸው ብሏል ጽህፈት ቤቱ፡፡ ንብረቶቹም ለጎንደር ጉምሩክ መቅረጫ ጣቢያ ገቢ እንደተደረጉ ነው የተገለጸው፡፡ ከተያዙት ንብረቶች ውስጥ 3 ሺህ 480 ህገ ወጥ የአሳ ማስገሪያ መረብ ይገኝበታል፡፡ ይህም መጠኑ ለማስገሪያነት ከሚያገለግለው መረብ ያነሰ በመሆኑ የአሳ ጫጩቶች ለምግነብነት ከመድረሳቸው እና ከመራባታቸው በፊት እንዲያዙ፣ የአሳ ምርትም እንዲቀንስ ያደርጋል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባህርዳር

የመስቀል በዓል ዘር፣ ቋንቋና ሃይማኖት ሳይለዩን በጋራ ተግባብተን መኖርን የተማርንበት ዕለት በመሆኑ በድምቀትና ታላቅ ኩራት ልናከብረው ይገባል ሲሉ የባህርዳር ሀገር ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብጹዕ አቡነ አብርሃም ገለጹ።

በየዓመቱ መስከረም 17 የሚከበረው የመስቀል በዓልን አስመልክቶ የሚካሄደው የደመራ ስነ-ስርዓት በርካታ ቁጥር ያላቸው ምዕመናንና የውጭ አገራት ቱሪስቶች በተገኙበት በባህርዳርና በሌሎች ከተሞችም በድምቀት ተከብሯል።

አቡነ አብርሃም በበዓሉ ላይ ለምዕመናን ባስተላለፉት መልዕክት ወቅቱ የመስቀሉ ባለቤት የሆኑ ክርስቲያኖች ፈተና የበዛበት በመሆኑ ይህን አስከፊ ጊዜ በትዕግስት ዕንጂ ጥፋትን በጥፋት በመመለስ መሆን እንደማይገባው ተናግረዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-27-3

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዛሬ የህዳር 10/2012 ዓ/ም በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ከሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባልት እና ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተሰባሰበ መረጃ👇
https://telegra.ph/ETH-11-20-4

(TIKVAH-ETHIOPIA)

#ድሬዳዋ #ሀረማያ #ወልዲያ #መቱ #ASTU
#መደወላቡ #ባህርዳር #ደባርቅ #ደብረታቦር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እግር ኳስ ለሰላም፣ ለፍቅር፣ ለአንድነት፣ ለአብሮነት፣ ለሀገር ግንባታ!

#ባህርዳር_ከነማ
#መቐለ70_እንደርታ

PHOTO : ጋንታ መቐለ 70 እንደርታ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ባህርዳር

የባህር ዳር ቲክቫህ አባላት ከለሊት 7:40 አካባቢ ሶስት ጊዜ የፍንዳታ ድምፅ እንደሰሙ ገልፀዋል።

አባላቶቻችን ከዚህ ቀደም የሰሙት አይነት ተመሳሳይ ፍንዳታ እንደሆነም ነው የገለፁት።

ፍንዳታውን ተከትሎ የተኩስ ድምፅ እንደነበርም ገልፀዋል።

ዝርዝር መረጃ በሚመለከታቸው አካላት ሲገለፅ ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
* 2 የችሎት ጉዳዮች !

#አዲስ_አበባ

የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠ/ኤታማዦር ሹም ጄነራል ሰዓረ መኮንንና ሜጀር ጄነራል ገዛኢ አበራን በመግደል በፍ/ቤት ጥፋተኛ የተባለው አስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ በሞት እንዲቀጣ ጠይቋል።

የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዛሬ አርብ ጥያቄውን ያቀረበው የአስር አለቃ መሳፍንትን የክስ ሂደት ለሚመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው። 

ዐቃቤ ህግ ዛሬ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ባለ 3 ገጽ የቅጣት አስተያየት፤ በተከሳሹ ላይ ሶስት የቅጣት ማክበጃዎችን ጠቅሷል።

የተከሳሽ ጠበቆች ፥ ተከሳሽ ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የለበትም ብለዋል። ዐቃቤ ህግ “አንድም [የወንጀል] ሪከርድ ሳያቀርብ የሞት ፍርድ መጠየቁ ከህጉ ያፈነገጠ ነው” ሲሉ የአቃቤ ህግን የቅጣት አስተያየት ተቃውመዋል። 

ፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለሰኔ 21 /2013 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በዝርዝር ያንብቡ : telegra.ph/Ethiopia-Insider-06-18

#ባህርዳር

ዛሬ አርብ ማለዳ የባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት የዋለው ችሎት በሰኔ 15ቱ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ግድያ እጃቸው አለበት የተባሉ 55 ተከሳሾች ላይ ብይን ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ በሻምበል መማር ጌትነት የክስ መዝገብ ስማቸው የተዘረዘሩ 55 ተከሳሾች ውስጥ 6ቱ በሌሉበት፣ 49 በተገኙበት ፍርዳቸው ሲታይ የነበረ ሲሆን ዛሬ ፍርድ ቤቱ 20ዎቹን በነጸ አሰናብቷል።

በነጻ እንዲሰናበቱ ከተበየነላቸው ተከሳሾች መካከል አቶ ዘመነ ካሴ ይገኙበታል።

በዝርዝር ያንብቡ : telegra.ph/BBC-06-18-2

መረጃዎቹ ከኢትዮጵያ ኢንሳይደር እና ከቢቢሲ የተውጣቱ ናቸው።

@tikvahethiopi
ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው ..

- ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣
- የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ
- የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ
- ወልዲያ
- ሪፍትቫሊ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በዛሬው እለት እያስመረቁ ነው።

#ባህርዳር_ዩኒቨርሲቲ

የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 363 ተማሪዎችን ነው እያስመረቀ የሚገኘው።

ተማሪዎቹ በመደበኛ፣ በተከታታይ እና በክረምት መርሐ-ግብሮች፤ በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ ዲግሪ፣ በሶስተኛ ዲግሪ እና የስፔሻሊቲ ህክምና የሰለጠኑ ናቸው።

#አሶሳ_ዩኒቨርሲቲ

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 237 ተማሪዎችን ነው በማስመረቅ ላይ የሚገኘው።

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ተማሪዎችን ሲያስመርቅ ለ8ተኛ ጊዜ ሲሆን የዛሬዎቹ ተመራቂዎች በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠኑ ናቸው።

#የኢትዮጵያ_ሲቪል_ሰርቪስ_ዩኒቨርሲቲ

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲም በተለያየ የትምህርት መስኮች በመደበኛ እና በተከታታይ የትምህርት መርሐ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ2 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎችን ነው እያስመረቀ የሚገኘው።

ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ ሁለተኛ ዲግሪ እና በፒ.ኤች.ዲ የተማሩ ናቸው።

ከእለቱ ተመራቂዎች ውስጥ 153 የሚሆኑት ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመሆን በውጭ ግንኙነት ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የሰለጠኑ እጩ ዲፕሎማቶች ናቸው።

#ወልዲያ_ዩኒቨርሲቲ

ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2,537 ተማሪዎችን አስመርቋል።

#ሪፍትቫሊ_ዩኒቨርስቲ

የሪፍትቫሊ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ ትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 16, 967 ተማሪዎች በአዲስ አበባ ስታዲየም አስመርቋል።

መረጃው የetv ነው።

@tikvahethiopia
#Bahirdar

በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር ከተማ ማታ ማታ የሚኒቀሳቀሱ ባጃጆች ቁጥር እንዲወሰን ተደረግ።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ወንጀል እንዳይከሰት ለመቆጣጠር ያመች ዘንድ እንደሆነ ተነግሯል።

እንደሀገር ሆነ እንደ ክልል የተከሰተውን የፀጥታ ሁኔታ በተገቢ መንገድ ለመምራት በባህር ዳር በህጋዊ መንገድ ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የባጃጅ ማህበራት ከከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ጽ/ቤት፣ ከፖሊስና መሰል የህግና የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር በሌሊት አገልግሎት የሚሰጡ ባጃጆች ተጠያቂነት ባለው አሰራር ታቅፈውና ለቁጥጥር እንዲያመች በቁጥር ተወስነው እንዲሰሩ መደረጉን የየማህበራቱ አስተባባሪዎች ተናግረዋል፡፡

በዚህ መሰረት ከስምንት የባጃጃ ማህበራት ውስጥ በስነ-ምግባር እና ለማህበረሰቡ ቅንና ታማኝ አገልግሎት ከሚሰጡ የባጃጅ አሽከርካሪዎች መካከል 120ዎችን በመመልመልና ከምሽቱ 3፡00 እስከ ንጋት 11፡00 ድረስ በሁሉም ቀበሌዎች እየተንቀሳቀሱ ከዛሬ ጀምሮ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል።

ይህ ለከተማው ሰላምና፣ ለማህበረሰቡ ደህንነት ሲባል የሚደረግ በመሆኑ የተመደቡ ባጃጆች ተጠያቂነት እንዲኖራቸው የማህበራቸውን ስምና አንፀባራቂ የደንብ ልብስ እንዲጠቀሙ፣ በዚያው ሰርጎ ገቦችን በመቆጣጠር በኩል ለሚደረገው ተግባር ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ መደረጉንም ገልፀዋል፡፡

ለዚህ ከተመደቡ ውጭ ማነኛውም ባጃጅ ከ3 ሰዓት ጀምሮ መንቀሳቀስ እንደሌለበትና ይህን ውሳኔ ተላልፎ የተገኘ የባጃጅ አሽከርካሪ ካለ በህግ ይጠየቃል ተብሏል።

የተመደቡት 120 ባጃጆች ያለምንም ዋጋ ጭማሪና ያለ አድሎ በሌለበት ሁኔታ እንዲሰሩ በሚሰጡት አገልግሎትም እጥረት ካለ እየተገመገመ እንደሚስተካከል ከ #ባህርዳር_ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#ባህርዳር

ነገ ባህር ዳር ከተማ የኢትዮጵያ እና የዚምባቡዌ የእግር ኳስ ፍልሚያን ታስተናግዳለች።

ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ወደጋና አቅንታ 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት መሸነፏ ይታወሳል፤ የነገው ጨዋታ ሁለተኛው የማጣሪያ ጨዋታ ነው።

ይህን ጨዋታ የምታስተናድገው ደግሞ ውቢቷ ባህር ዳር ከተማ ናት።

የነገው ጨዋታ ኮሚሽነር ከኤርትራ ፤ የዳኞች ገምጋሚ ከኮትዲቫር ፤ አራቱም የጨዋታ አመራሮች ከሲሼልስ ናቸው።

በነገው ፍልሚያ ብሄራዊ ቡድናችን የተለመደውን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የሚለብስ ይሆናል።

የኢትዮጵያና የዚምባቡዌ ብሄራዊ ቡድኖች በነገው እለት የሚያደርጉት ጨዋታ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለካፍ ጥያቄ ቢያቀርብም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ፍቃደኛ ባለመሆኑ ጨዋታው ያለተመልካች እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዛሬ ምሽት አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#ሀዋሳ #ድሬዳዋ #ባህርዳር

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የማለዳ በረራ ጀመረ።

አየር መንገዱ ከሀዋሳ ፣ ከድሬዳዋ እና ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ ማለዳ 1:00 የሚነሱ እለታዊ በረራዎች መጀመሩን አሳውቋል።

#EthiopianAirlines

@tikvahethiopia
#ባህርዳር_ዩኒቨርሲቲ

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና ለኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ ነው።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በሃይማኖት አባትነታቸው የተማሩትንና ያስተማሩትን በተግባር ለሚኖሩት፤ ሰውን በሰውነቱ ብቻ ላከበሩት ታላቁ ብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና  ኢትዮጵያን ብሎም አፍሪካን በስፖርቱ ዓለም በማስጠራት ጀምራ ለኅብረሰተብ ፍቅርና አንድነት መጎልበት ለምትተጋው ኮሎኔል አትሌት ደራርቱ ቱሉ የዓመቱን የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ መሆኑን ዛሬ አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬቱን የሚያበረክተው ነሐሴ 21 ቀን 2014 በሚያካሂደው የተማሪዎች ምረቃ ላይ ነው።

@tikvahethiopia