TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Somalia

አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በዓለ ሲመታቸው ይከናወናል።

ለዚህም በዓለ ሲመት የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ወደ ሶማሊያ ሞቃዲሾ በመግባት ላይ ይገኛሉ።

ዛሬ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከልዑካቸው ጋር ሞቃዲሾ ገብተዋል።

በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በተመራው የልዑካን ቡድን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ፣ የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ ይገኙበታል።

ዶ/ር ዐቢይ ዛሬ ሞቃዲሾ ከገቡ በኃላ ከፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ጋር መገናኘታቸውን የሶማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሶማሊያ በሚኖራቸው ቆይታ በፕሬዝደንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በዓለ ሲመት ላይ ንግግር እንደሚያርጉ ፤ በተጨማሪም በበዓለ ሲመቱ ከሚታደሙ ከሌሎች የሀገራት መሪዎች ጋር የሁለትሽ ምክክር እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።

ፎቶ ፡ Ahmed K Kosar / Somali Guardian

@tikvahethiopia
#Somalia

የግብፁ " Banque Misr " እና የቱርኪዬ " Ziraat Katilim " ባንኮች ሶማሊያ ውስጥ እንዲሰሩ ፍቃድ ፀደቀላቸው።


ጎረቤት ሶማሊያ ለግብፅ እና ቱርኪዬ ባንኮች የስራ ፍቃድ አፅድቃለች።

የሶማሊያ ማዕከላዊ ባንክ ቦርድ ትላንት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ መስፈርት አሟልተው ለተገኙት ሁለት ዓለም አቀፍ ባንኮች በሀገሪቱ ውስጥ ቅርጫፎቻቸውን እንዲመሰርቱ እና እንዲንቀሳቀሱ ፍቃድ አፅድቋል።

ፍቃዱ ረጅም ወራት ከወሰደ ሂደት በኃላ ነው የፀደቀው።

ፍቃድ የፀደቀላቸው ባንኮች የግብፁ " Banque Misr " እና የቱርኩ " Ziraat Katilim " ሲሆኑ በሶማሊያ የፋይናንስ ሴክተር እና በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ፍቃዱን ያፀደቀው CBS ገልጿል።

ሁለቱ ባንኮች ሶማሊያ ውስጥ እንዲሰሩ ፍቃድ ያገኙ #የመጀመሪያዎቹ ዓለም አቀፍ ባንኮች ሆነው ተመዝገበዋል።

@tikvahethiopia
#Somalia

አልሸባብ ዛሬ #ሶማሊያ ውስጥ ባደረሰው ጥቃት የሰዎች ህይወት ጠፋ።

በሽብር ቡድኑ በሶማሊያ ደቡባዊ አቅጣጫ በተለያዩ ቦታዎች በተፈፀሙ ሁለት የቦንብ ጥቃቶች በርካቶች ተገድለዋል።

በመጀመርያው ጥቃት ታችኛው ሸበሌ ክልል በአፍጎዬ ከተማ በእንስሳት የገበያ ቦታ በተወረወሩ 2 ቦምቦች በትንሹ 4 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን ተነግሯል።

ሁለተኛው ጥቃት ማርካ በተባለችው የወደብ ከተማ የተፈፀመ ሲሆን የወረዳው ኮሚሽነር አብዱላሂ አሊ ዋፎው በጥቃቱ መገደላቸው ተዘግቧል።

ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል።

የአካባቢው ፖሊስ እንዳስታወቀው ጥቃቱ የተፈፀመው የማርክ ወረዳ ኮሚሽነር በወረዳዉ ጽሕፈት ቤት ቅጥር ግቢ ዉስጥ ለተሰበሰቡ ነዋሪዎች ንግግር ሲያደርጉ ነው።

ንግግር ሲያደርጉ የነበሩት ኮሚሽነሩ አብዱላሒ ዓሊ አሕመድ ዋፎው እና ሌሎች ስምንት ተሰብሳቢዎች ወዲያዉ ሞተዋል።

ምንጭ፦ ሮይተርስ እና ዶቼ ቨለ

@tikvahethiopia
#Somalia #SW

ሀሰን ኢብራሂም ሉግቡር ተገደሉ።

የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ክልል ፍትህ ሚኒስትር ሀሰን ኢብራሂም ሉግቡር በባይዶዋ ከነ ልጃቸው በአጥፍቶ ጠፊ የቦንብ ጥቃት ተገደሉ።

ሚኒስትሩ የተገደሉት ዛሬ ዓርብ ዕለት ከመስጂድ ሲወጡ በተፈፀመ ጥቃት ነው።

በጥቃቱ ሌሎች 11 ሰዎችም ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።

የደቡብ ምዕራብ ክልል ፕሬዜዳንት አብዲአዚዝ ሀሰን ሞሀመድ ግድያውንና ጥቃቱን አውግዘው ከጥቃቱ ጀርባ የአልሸባብ የሽብር ቡድን መኖሩን አመልክተዋል።

ይህ ጥቃት በያዝነው ወር እኤአ በቀን 27 በታችኛው ሸበል ክልል የማርካ ወረዳ አስተዳዳሪ አብዱላሂ አሊ ዋፎውን ጨምሮ ከ10 በላይ ሰዎችን ከገደለው የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት እንዲሁም በአፍጎዬ ከተማ ፍንዳታ ተከስቶ ቢያንስ አራት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ከቆሰሉበት ጥቃት ከቀናት በኃላ የተፈፀመ ነው።

በሌላ በኩል፤ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ዛሬ #ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰነው የሶማሊያዋ የድንበር ከተማ " አቶ " ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት ከፍቶ እንደነበር ቢቢሲ ሶማልኛ ዘግቧል።

አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልወደዱ የሶማሌ ክልል ባለሥልጣን በሰጡት ቃል ፤ የሽብር ቡድኑ አቶ ላይ በ2 ሳምንት ውስጥ ለ2ኛ ጊዜ ጥቃት መሰንዘሩን ይህን ተከትሎ ውጊያ መካሄዱን አመልክተዋል።

ዛሬ ወደ አቶ ዘልቆ ጥቃት የመፈጸም ዓላማ የነበረው የአልሻባብ ታጣቂ ኃይል፤ ያሰበው ሳይሳካ #ሽንፈት እንዳጋጠመው ተናግረዋል።

በፀጥታ ኃይሎችም በኩል ጉዳት መድረሱን ያመለከቱት ባለስልጣኑ ለጊዜው ዝርዝር መናገር አልችልም ብለዋል።

አልሸባብ ከጥቂት ቀናት በፊት ኢትዮጵያን ለመዳፈር ሞክሮ በሶማሌ ልዩ ኃይል ክፉኛ መመታቱ አይዘነጋም። አሁንም በድንበር የተጠናከረ ጥበቃ መኖሩን ለማወቅ ችለናል።

@tikvahethiopia
#Somalia

የአልሸባብ ታጣቂዎች ተገደሉ።

ዛሬ ቅዳሜ በሶማሊያ ቤይ ክልል ባርዳሌ ወረዳ ስር በሚገኘው " ቶስዌይን መንደር " አቅራቢያ የአልሸባብ ታጣቂዎች ተገድለዋል።

የሶማሌ ብሄራዊ ጦርና የሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት የክልል ጦር በአልሸባብ አሸባሪዎች ላይ ባካሄደው የማጥቃት እርምጃ ሶስት የቡድኑ ታጣቂዎች መገደላቸውን የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USAirstrike የአሜሪካ አየር ጥቃት - በጎረቤት ሶማሊያ ! በጎረቤታችን ሶማሊያ ሂራን ክልል የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር ኃይል የፀረ ሽብር ዘመቻ እያካሄደ ሲሆን ጦሩን ለመደገፍ #አሜሪካ የአየር ጥቃት መሰንዘር መጀመሯ ተገልጿል። አሜሪካ የአየር ላይ ጥቃቱን እንድትሰነዝር የተጠየቀችው በሶማሊያ መንግስት መሆኑን የሀገሪቱ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል። በክስተቱ ንፁሀን ዜጎች ላይ ምንም አይነት…
#US #SOMALIA

አሜሪካ ትላንትና ማክሰኞ ፤ ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመተባበር በፈፀመችው የአየር ድብደባ 4 የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባላትን መግደሏን አሳውቃለች።

የአልሸባብ ታጣቂዎች የሶማሊያ ጦር ላይ በቤልድዌይኔ ጥቃት የከፈቱ ሲሆን ይህን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር በአየር በፈፀመው ድብደባ 4 የቡድኑን አባላት መግደሉ ተገልጿል።

አሜሪካ እርምጃው በሶማሊያ መንግስት በኩል ፍቃድ ኖሮት መፈፀሙን አሳውቃለች።

በጥቃቱ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ / ሲቪሎች እንዳልተገደሉ ተመላክቷል።

@tikvahethiopia