TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች፦

- ሼንዠን ውሻና ድመት ለምግብነት እንዳይውሉ ያገደች የመጀመሪያዋ የቻይና ከተማ ሆናለች።

- በሊባኖስ የፊሊፒንስ አምባሳደር በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቅተው መሞታቸው ተሰምቷል።

- በሩስያ ተጨማሪ 6 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መሞታቸው ተሰምቷል።

- በዓለም ላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ950,000 በልጧል። ከ48,000 በላይ ሰዎች ሞተዋል፣ ከ200,000 በላይ ሰዎች አገግመዋል።

- በዓለም ላይ የኮቪድ-19 ተጠቂ 1 ሚሊዮን ሊደርስ በተቃረበበት ወቅት ሰሜን ኮሪያ አሁንም አንድም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ በሀገሬ የለም ብላለች።

- የሩዋንዳ መንግሥት የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ስርጭትን ለመቆጣጠር ተግባራዊ ያደረገውን ጥብቅ ከቤት ያለምውጣት ክልከላ ለተጨማሪ 3 ሳምንታት አራዝሟል።

- በአውሮፓ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ግማሽ ሚሊዮን ደርሷል።

- በስፔን በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ10,000 በልጣል። በ24 ሰዓት የ950 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል።

#SkyNews #BBC #Euronews #Aljazeera

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች፦

- የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በአገሪቱ የጣሉትን በቤት የመቀመጥ ውሳኔ በአንድ ወር አራዝመዋል

- እስካሁን ቫይረሱ ሀገሯ ሳይገባ የቆየችው ማላዊ በዛሬው ዕለት ሶስት ኬዞችን ሪፖርት አድርጋለች።

- የኢራን ፓርላማ አፈጉባኤ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በምዕራብ አፍሪካ የነበሩ 3 የፈረንሳይ ወታደሮች በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ተሰምቷል። ወታደሮቹ ወደፈረንሳይ እንዲመለሱም ተደርጓል።

- በጣልያን በ24 ሰዓት ውስጥ የ760 ሰዎች ሞት ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 13,915 ደርሷል። በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥርም ከ115,000 በልጧል።

- በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 5,626 ደርሰዋል። 235,860 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል።

- በመላው ዓለም የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በልጧል። ከ51,000 በላይ ሰዎችም ሞተዋል። 210,308 ሰዎች ደግሞ አገግመዋል።

-ሳዑዲ አረቢያ የ24 ሰዓት የሰዓት እላፊ በቅዱስ ከተሞቿ ላይ ጥላለች። በመካ እና በመዲና የተጣለው የሰዓት እላፊ የኮሮናቫይረስን ስርጭት ለመከላከል ነው ተብሏል።

#SkyNews #BBC #Euronews #Aljazeera

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው!

በአለም አቀፍ ደረጃ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ2,000,000 በላይ ሆኗል። ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 485,304 ሺህ ደሷል። የሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 126 ሺህ 811 ደርሷል፡፡

- ዩናይትድ ስቴትስ እስካሁን ባለው መረጃ ከ614 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎቿ በዚሁ በሽታ ሲያዙ ከ26 ሺህ በላይ ያህሉ ህይወታቸውን አጥተዋል። በትላንትናው እለት ብቻ በአሜሪካ 2 ሺህ 385 ሰዎች በበሽው ሂወታቸው አልፏል፡፡

- በካናዳ የሟቾች ቁጥር ከ900 በልጧል። ባለፉት 24 ሰዓት 123 ሰዎች ሞተዋል። በሀገሪቱ በቫይረሳ የተያዙ ሰዎች ደግሞ ከ27 ሺህ በላይ ሆኖ ተመዝግባል፤ ከዚህ መካከል 1,383 የሚደርሰው ኬዝ በአንድ ቀን የተመዘገበ ነው።

- በቱርክ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች እየጨመረ ነው። ባልፉት 24 ሰዓት 4,062 አዲስ ኬዝ ሲመዘገብ፤ 107 ሰዎች ሞተዋል።

- በተመሳሳይ በሩሲያም ቫይረሱ በፍጥነት እየተስፋፋ ነው፤ ባለፉት 24 ሰዓት 2,774 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

- በአፍሪካ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ ሲሆን እስካሁን ድረስ ከ15 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፡፡ በአፍሪካ የሟቾች ቁጥር ደግሞ 790 ደርሷል።

#ETHIOFM #BBC #AFP #SKYNEWS
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia