TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#GERD

" ... በወንዞቻችን ለመጠቀም እና ድህነትን ለማስወገድ የምናደርገው ጥረት እራሳችንን እና ጎረቤቶቻችንን ጭምር ለመጥቀም እንጂ ማንንም ለመጉዳት እንዳልሆነ ለዓባይ ልጆች ሁሉ ለማረጋገጥ እፈልጋለሁ " - የቀድሞ የሀገራችን ጠ/ሚ ሀኃይለማርያም ደሳለኝ

@tikvahethiopia
#GERD

" ... የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንጨርሰዋለን። የታላቁ ህዳሴ ግድብን የምንጨርሰው ልጆቻችንን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስም እንደምንችል እንዲያውቁት ስለምንፈልግም ጭምር ነው " - የአሁኑ የሀገራችን ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ItsMyDam

የቀድሞ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ስመኘው በቀለ የተናገሩት ፦

" በዚህ ዘመን ላለነው ትውልድ አይደለም ለኢትዮጵያውያኖች ፣ ለትውልደ ኢትዮጵያውያኖች፣ በውጭ ለሚኖሩ ዜጎች ብቻ ሳይሆን ለመላው የዓለም ህዝብ የተለየ ልዩ መልዕክት እያስተላለፈ ያለ ፕሮጀክት ነው።

በአጠቃላይ ሀገራችንን በተለየ ገፅታ እንድትታይ (በበጎ መልኩ) ፣ በአጠቃላይ ትውልድ በስራ የሚያምን እንዲሆን ፣ በስራ የሚያምን ትውልድ ፣ በእራሱ የሚተማመን ትውልድ መፍጠር የቻለ ፕሮጀክት ነው።"

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አስተያየት ስጡበት ! የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን የዕጩ ኮሚሽነሮች ላይ ህዝቡ አስተያየት እንዲሰጥባቸው ምክር ቤቱ ዝርዝራቸውን ዛሬ ይፋ አድርጓል። በተለያዩ አግባቦች በተጠቆሙት 42 የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እጩ ኮሚሽነሮች ላይ ከዛሬ ጀምሮ የህዝብ አስተያየት ይሰበሰባል። ይህን 👉http://www.hopr.gov.et/am/web/guest/dialog-candidate ማስፈንጠሪያ በመጫን…
#Update

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል።

ምክር ቤቱ በስብሰባው የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን በኮሚሽነርነት የሚያገለግሉ የ11 ግለሰቦችን ሹመት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በአፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አማካኝነት ለም/ቤቱ ከቀረቡ ተሿሚዎች መካከል፤ ኮሚሽኑን በሰብሳቢነት እንዲመሩ የታጩት ፕ/ር መስፍን አርአያ ናቸው።

ወ/ሮ ሂሩት ገ/ስላሴ ደግሞ የምክክር ኮሚሽኑ ምክትል ሰብሳቢ እንዲሆኑ መመረጣቸውን ለፓርላማ አባላት በታደለ የተሿሚዎች ዝርዝር ላይ መስፈሩን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

የተሿሚዎች ዝርዝር ፦

1ኛ. ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ (ሰብሳቢ)
2ኛ. ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ (ምክትል ሰብሳቢ)
3ኛ. ዶ/ር አይሮሪት መሐመድ
4ኛ. ዶ/ር ተገኝወርቅ ጌቱ
5ኛ. ዶ/ር ዮናስ አዳዬ
6ኛ. ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ
7ኛ. አምባሳደር መሐመድ ድሪር
8ኛ. ወ/ሮ ብሌን ገብረመድህን
9ኛ. አቶ ዘገየ አስፋው
10ኛ. አቶ መላኩ ወልደማርያም
11ኛ. አቶ ሙልጌታ አጎ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ እያካሄደ ይገኛል። ምክር ቤቱ በስብሰባው የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን በኮሚሽነርነት የሚያገለግሉ የ11 ግለሰቦችን ሹመት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። በአፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ አማካኝነት ለም/ቤቱ ከቀረቡ ተሿሚዎች መካከል፤ ኮሚሽኑን በሰብሳቢነት እንዲመሩ የታጩት ፕ/ር መስፍን አርአያ ናቸው። ወ/ሮ ሂሩት ገ/ስላሴ ደግሞ…
#Update

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የሚመሩ 11 ኮሚሽነሮችን ሹመት በ5 ድምፀ ታአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል።

በዚህ መሰረት ፦

1ኛ. ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ (ሰብሳቢ)
2ኛ. ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ (ምክትል ሰብሳቢ)
3ኛ. ዶ/ር አይሮሪት መሐመድ
4ኛ. ዶ/ር ተገኝወርቅ ጌቱ
5ኛ. ዶ/ር ዮናስ አዳዬ
6ኛ. ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ
7ኛ. አምባሳደር መሐመድ ድሪር
8ኛ. ወ/ሮ ብሌን ገብረመድህን
9ኛ. አቶ ዘገየ አስፋው
10ኛ. አቶ መላኩ ወልደማርያም
11ኛ. አቶ ሙልጌታ አጎ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክርን በኮሚሽነርነት እንዲመሩ ተሹመዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የሚመሩ 11 ኮሚሽነሮችን ሹመት በ5 ድምፀ ታአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል። በዚህ መሰረት ፦ 1ኛ. ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ (ሰብሳቢ) 2ኛ. ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ (ምክትል ሰብሳቢ) 3ኛ. ዶ/ር አይሮሪት መሐመድ 4ኛ. ዶ/ር ተገኝወርቅ ጌቱ 5ኛ. ዶ/ር ዮናስ አዳዬ 6ኛ. ዶ/ር አምባዬ ኦጋቶ 7ኛ. አምባሳደር…
ፕ/ር መሰፍን አርአያ ወልደተንሳይ ማናቸው ?

የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት ዛሬ ፀድቋል። የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት ደግሞ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ናቸው።

• በሕክምና የዶክተሬት ዲግሪ ( MD) ፣ ከፓቭሎቭ ዩኒቨርሲቲ ሩሲያ፤

• በሳይኮቴራፒ ፍልስፍና የፒኤች ዲ ዲግሪ (PhD)፣ ከኦማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰዊድን፤

• ስፔሻላይዝድ ድፕሎማ፤ በሳይኮሎጂካል ሜድስን እና ሳይካትሪ፣ ግሮኒጎኝ ዩኒቨርስቲ ኔዘርላንድስ፣

• በኤፒዲሞሎጂና ባዮስታትስቲክስ ሰርተፍኬት፤ ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ የሥራ ልምድ፤

• ለ6 ዓመታት በዓዲግራት በደሴ እና በአማኑኤል ሆስፒታሎች ሜዲካል ኦፊሰርና ዳይሬክተር፤

• ለ10 ዓመታት በአማኑኤል ሆስፒታል ሳይካትሪስት፤

• ለ6 ዓመታት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ፕሮቮስት፤

• ለ6 ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሳይካትሪ ዲፓርትመንት ዲን፣

• ለ12 ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር ሆነው ፣ የዲፓርመንት ሃላፊ እና ልክቸረር ሆነው ካገለገሉ በኋላ ሙሉ የፕፌሰርነት ማዕረግ አግኝተዋል።

• ለ11 ዓመታት የፌደራል ሆስፒታሎች አመራር ቦርድ አባል፤

• በአሁን ወቅት ከሙያዊ አገልግሎት በተጨማሪ በኢፌዴሪ የማንነትና የአስተዳር ወሰን ኮሚሽን አባል ሆነው ያገለግላሉ።

ምንጭ፦ የህ/ተ/ም/ቤት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕ/ር መሰፍን አርአያ ወልደተንሳይ ማናቸው ? የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት ዛሬ ፀድቋል። የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት ደግሞ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ናቸው። • በሕክምና የዶክተሬት ዲግሪ ( MD) ፣ ከፓቭሎቭ ዩኒቨርሲቲ ሩሲያ፤ • በሳይኮቴራፒ ፍልስፍና የፒኤች ዲ ዲግሪ (PhD)፣ ከኦማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰዊድን፤ • ስፔሻላይዝድ ድፕሎማ፤ በሳይኮሎጂካል ሜድስን እና ሳይካትሪ፣…
ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ ኦዳ ማን ናቸው ?

የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ሆነው ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ ተሹመዋል።

• በህግ ሜትሪዝ ምሩቅ ሰርቦን ዩኒቨርሲቲ (ፈረንሳይ)

• ለ2 ዓመት በህግ እና ፍትህ ሚኒስቴር የህግ ተንታኝ ባለሞያ

• ለ2 ዓመት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስር የአፍሪካ ህብረት የህግ ጥናት ኦፊሰር

• ለ2 ዓመት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ሌክቸረር

• ለ8 ዓመት በግል የንግድ ድርጅት ከፍተኛ የህግ አማካሪ

• ለ4 ዓመት በዓለም አቀፍ የንግድ አማካሪ በመሆን ለUN ፣ World Bank) ፣ OAU የጥናት እና የማማከር ስራ

• ለ6 ዓመታት የአፍሪካ የሴቶች የሰላምና ልማት ኮሚቴ ከፍተኛ ኦፊሰር

• ለ3 ዓመት በኦክስፋም አህጉራዊ የሰላም ግንባታ እና የግጭት አመራር አማካሪ

• 14 ዓመት በተለያዩ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች የሰሩ፣ ለምዕራብ አፍሪካ እና ሳህል የተባበሩት መንግስታት ዋና ፀሐፊ ምክትል ወኪል ሆነው እያገለገሉ ያሉ

ምንጭ፦ የህ/ተ/ም/ቤት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ጡረታ እንደሚወጡ ማሳወቃቸውን ተከትሎ አሜሪካ በአዲስ አበባ ለሚገኘው ኤምባሲ አዲስ ሰው በተወካይነት በኃላፊነት ቦታ ላይ መድባለች። አሜሪካ በአዲስ አበባ ላለው ኤምባሲዋ ትሬሲ አን ጃኮብሰንን ነው በጊዜያዊነት በኃላፊነት ቦታ ላይ ያስቀመጠችው። አሜሪካዊቷ ዲፕሎማት ትሬሲ አን ጃኮብሰን በቱርክሜኒስታን፣ ታጂኪስታንና ኮሶቮ የአሜሪካ አምባሳደር…
ጊታ ፓሲ ተሰናበቱ።

ፕሬዚደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደር ጊታ ፓሲ ዛሬ አሰናበቱ።

አምባሳደሯ የሹመት ደብዳቤያቸውን ከአንድ ዓመት በፊት የካቲት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ማቅረባቸው እንደሚታወስ ከፕሬዚደንት ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያሳያል።

አምባሳደር ጊታ ፓሲ ጡረታ እንደሚወጡ ማሳወቃቸውን ተከትሎ አሜሪካ በአዲስ አበባ ለሚገኘው ኤምባሲዋ ትሬሲ አን ጃኮብስን በጊዜያዊነት በኃላፊነት ቦታ ላይ መመደቧ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#አሳትፉን
#ህጉ_የኔም_ነው_ይመለከተኛል

ኤቲኤሞች ለአካል ጉዳተኞችተደራሽ ናቸው ?

በአዲስ አበባ ውስጥ የምናገኛቸው አብዛኛዎቹ ኤቲኤምዎች ለአካል ጉዳተኞች ሙሉ በሙሉ ተደራሽ አለመሆናቸውን ሲቪል ሶሳይቲ ሪሶርስ ሴንተር ከCSSP2 ጋር በመተባበር አዘጋጅቶ በላከልን መልዕክት አሳይቷል።

ይህ ሁኔታ እንዲስተካከልና ሁሉም አካል ጉዳተኞች የህዝብ አገልግሎት የማግኘት ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው እንዲከበር ጠይቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሳምሶን ተክለሚካኤል እስካሁን ያለበት አልታወቀም፤ የት ነው ያለው ? ኢትዮጵያ የኬንያ ባለስልጣናትን ናይሮቢ ውስጥ መሀል መንገድ ላይ ስለታገተው ሳምሶን ተክለሚካኤል ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቃለች። በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር መለስ አለም ኬንያ ለሚገኝ የሃገር ውስጥ ሚዲያ በሰጡት ቃለ ምልልስ የኬንያ የህግ አስከባሪ አካላት በንግድ ስራ ላይ የተሰማራው ሳምሶን ተክለሚካኤል የት እንዳለ እንዲሁም በምን…
ሳምሶን የት ነው ያለው ?

በኬንያ መዲና ናይሮቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከወራት በፊት ታፍኖ የተወሰደው አቶ ሳምሶን ተክለሚካኤል የት እንዳለ እስካሁን ድረስ አለመታወቁን በመቃወም ሰልፍ አካሂደዋል።

ከሦስት ወራት በፊት ከናይሮቢ ጎዳና ላይ ባልታወቁ ሰዎች ከመኪናው እንዲወርድ ተደርጎ ከተወሰደ በኋላ እስካሁን ያለበት ያልታወቀው በንግድ ሥራ የሚተዳደረው አቶ ሳምሶን ጉዳይ ያሳሰባቸው ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ እንዲሁም ሌሎችም በናይኖቢ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ናቸው ሰልፉን ያካሄዱት።

- ፍትሕ ለሳሚ !
- ሳሚ የት ነው ?
- ባለቤቴ ሳሚ የት ነው ?
- ጓደኛዬ ሳሚ የት ነው ?
- አጎቴ ሳሚ የት ነው ? የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን ይዘው ኢትዮጵያውያኑ ሰልፍ ወጥተዋል።

የአቶ ሳምሶን ባለቤት ወ/ሮ ሚለን ሃለፎምን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶች እና ወጣቶች በናይሮቢ አደባባይ ወጥተው ድምጻቸውን አሰምተዋል።

አቶ ሳምሶን በዚህ ዓመት ኅዳር መጀመሪያ ላይ ነበር በናይሮቢ ከተማ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ከመንገድ ላይ በኃይል ከተወሰደ በኋላ እስካሁን ድረስ ያለበት አልታወቀም።

ከሳምንታት በፊት ለኬንያ ሚዲያዎች ቃላቸውን የሰጡት በኬንያ የኢትዬያጵያ አምባሳደር መለስ አለም ፥ "የኬንያ መንግሥት እና የሕግ አካላት ሳምሶን የት እንዳለ እንዲያሳውቁን ጠይቀናል" ማለታቸው አይዘነጋም።

አቶ ሳምሶን ታፍኖ የተወሰደ ሰሞን የኬንያ ፖሊስ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለው እንደሆነ የገለጸ ቢሆንም፤ እስከ ዛሬ ግን ከኬንያ ፖሊስ ሆነ ከኬንያ መንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕ/ር መሰፍን አርአያ ወልደተንሳይ ማናቸው ? የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮችን ሹመት ዛሬ ፀድቋል። የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ሆነው የተመረጡት ደግሞ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ናቸው። • በሕክምና የዶክተሬት ዲግሪ ( MD) ፣ ከፓቭሎቭ ዩኒቨርሲቲ ሩሲያ፤ • በሳይኮቴራፒ ፍልስፍና የፒኤች ዲ ዲግሪ (PhD)፣ ከኦማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰዊድን፤ • ስፔሻላይዝድ ድፕሎማ፤ በሳይኮሎጂካል ሜድስን እና ሳይካትሪ፣…
#አገራዊ_ምክክር

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰብሳቢ ፕ/ር መስፍን አርአያ ከሹመቱ በኃላይ የተናገሩት ፦

" አስራ አንዳችንም ገና በሚገባ መተዋወቅ አለብን። እዚህ ውስጥ በተለይ አስሩ በጣም ብዙ ልምድ ያላቸው ናቸው። ደስ ብሎኛል ሴቶች አሉ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ፤ ወጣቶች አሉ።

በእርግጥ በተወካይነቱ ላይ ኢትዮጵያ ከ86 ብሄረሰቦች በላይ ነው ያሏት ስለዚህ 86ቱንም ወደዚህ ማምጣት ሳይሆን 86ቱና ከዚያ በላይ ያሉትን ወደ መግባባት መድረኩ ማምጣት ስለሆነ ትልቁ ስራ እንግዲህ በጋራ ስንገናኝ ስራ ስንከፋፈል የምናየው እና የምናውቀው ይሆናል።

ይሄ ኃላፊነት ከሌሎች ኃላፊነት ለየት ሚያደርገው የመግባባት አጀንዳዎች በጣም ብዙ ናቸው። ስለዚህ እነዚህ አጀንዳዎች ነቅሶ ወደ ጠረጴዛ በማምጣት አጀንዳዎቹ ላይ በትክክል በጋራ፣ በኢትዮጵያዊነት ላይ ፣ መብትን በማስከበር ላይ ፣ ባህልን ፣ ቋንቋን እና ሌሎችንም የሚመለከታቸውን ነገሮች በማስከበር ላይ ትልቅ ብሄር ትንሽ ብሄር ሳንል ሁላችንም በጋራ መስራቱ ላይ ብዙ ነገር ስለሚጠበቅብን ይሄ ትልቅ ኃላፊነት ነው ብዬ አስባለሁ፤ ደግሞም ነው ይሄ ነው ከበድ ያደርገዋል ብዬ የማስበው።

በጋራ ከሰራን ወደ መፍትሄ የማንደርስበት ምክንያት የለም። ሁሉም ነገር ሰልችቶናል ሰላም ማጣቱና መጎዳቱ እና መብት በማስከበር ሂደቱ ላይ የደረሰብን ብዙ ጉዳዮች ስላሉ እነኛን በጋራ እንፈታለን ብዬ አስባለሁ።

ሀገርን በመገንባቱ ሂደት፣ ህዝብን ወደመግባባቱ በማምጣት ሂደት ሚዲያዎች ትልቅ ቦታ አላቸው ፣ፖለቲካ ፓርቲዎች ፣የሃይማኖት አባቶች ፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ አባገዳዎች እና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ወጣቶች በተለይ በዚህ ስራ ላይ ከጎናችን ሆነው ይረዱናል ያግዙናል ወደ መፍትሄ ያመጡናል ብዬ አስባለሁ "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አገራዊ_ምክክር

የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ወ/ሮ ሂሩት ገብረስላሴ ከሹመቱ በኃላ የተናገሩት ፦

"... ሌላ ዓለም ላይ ሰርቻለሁ። ሌላ ዓለም ላይ ያለኝን እውቀት ፣ ያለኝን ልምድ ተጠቅሜ ነው ኢትዮጵያ ላይ ሲሆን ሀገሬ ስለሆነ እንደ ሚሽንም ነው ከፍተኛ ስሜትም አለው። ከእኔም ከሁላችም ከፍተኛ ቁርጠኝነት ይኖራል ብዬ አስባለሁ።

ትልቅ ኃላፊነት ነው የተሰጠን ፤ ትልቅ ክብርም ነው ግን የተሰጠን ለዛ ብቁ ሆነን ለመገኘት ማድረግ ያለብንን ጥረት እናደርጋለን።

... የዚህች ሀገር ችግር የህዝቦች ችግር አይደለም የኤሊቱ ፣ ተምሪያለሁ ባይ ፣ አንድ ቦታ ደርሻለሁ ባይ የኤሊቱ ችግር ስለሆነ ለኤሊቱ ነው ጥሪ ማቅረብ ያለብን ኤሊቱ ላይ ነው በጣም መሰራት ያለበት ህዝቡ መኖር ነው የሚፈልገው፤ በሰላም መኖር ነው የሚፈልገውና የህዝቡ ችግር አይደለም። ስለዚህ ማሸነፍ የሚኖርብን ኤሊቱን ነው።

እዚህች ሀገር ላይ ኤሊት መሆን ማለት እኮ Privileged የሆነ status አለህ ማለት ነው። የተሻለ ትምህርት አግኝተሃል ፣ የተሻለ ኑሮ ኖረሃል ፣ የተሻለ Experience አለህ ተብሎ የሚገመት የማህበረሰብ ክፍል አስቸጋሪ ሆኖ ሊቀጥል አይገባውም ፤ አይችልም።

እኔ ይመስለኛል እግዚአብሔር ከረዳን አንድ ቦታ እንደርሳለን። "

@tikvahethiopia