TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኮማንደር ዋለልኝ⬆️"እስካሁንም በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ ምንም አይነት የመገናኛ ሬዲዮም ሆነ ቦምብ የለም።”

#BahirDar #ባህር_ዳር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BAHIRDAR

የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት በየአጥቢያዎቹ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ጸሎተ ምህላ አወጀ፡፡ ሀገረ ስብከቱ ለመስከረም 11 ቀን 2012 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ከፊታችን ሰኞ መስከረም 5 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ጸሎተ ምህላ አውጇል፤ ለመስከረም 11 ቀን 2012 ዓ.ም ደግሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ ሀገረ ስብከቱ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመላከተው የፀሎተ ምህላው ዓላማ በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ የሚደርሰውን መከራ፣ ግፍ እና መሰደድ አስመልክታ ለፈጣሪዋ መልዕክት ለማቅረብ ነው፡፡

ከጸሎተ ምህላው እና ከሰልፉ በኋላ በእለቱ 10፡00 ሰዓት ላይ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ስለወቅታዊው የቤተ ክርስቲያን ጥያቄ ውይይት ይደረጋል ተብሏል በመግለጫው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BAHIRDAR_INDUSTRIAL_PARK

የባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የመጀመሪያው የግንባታ ምእራፍ ተጠናቆ በመስከረም ወር መጨረሻ ሥራ እንደሚጀምር የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ገለፀ።

የኮርፖሬሽኑ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አማረ አስገዶም እንደገለፁት፣ የፓርኩ የመጀመሪያው ምእራፍ ግንባታ በ75 ሄክታር መሬት ላይ በውሉ መሰረት በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል። በዚሁ ምእራፍ የተገነቡት የፋብሪካ ሼዶችም ስምንት ሲሆኑ፣ በመጀመሪያው ዙር ለአራት ሺ በሁለተኛው ዙር ደግሞ ለስምንት ሺ ዜጎች የሥራ እድል ይፈጥራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ፤ በመጀመሪያው ምእራፍ የፓርኩ ግንባታ የሚያስፈልገው የኃይል መጠን ስምንት ሜጋ ዋት በመሆኑ በኃይል አቅርቦቱ ዙሪያ ጥናት ተሰርቶ ተጠናቋል። የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰጪ አካሉም የኤሌክትሪክ ምሰሶ ተከላዎችን ጀምሯል። በዚህ ወር መጨረሻም ለፓርኩ የሚያስፈልገው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ይቀርባል ተብሎ ይታሰባል።

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BAHIRDAR

"የባህር ዳር ነዋሪ ነኝ ፍርድ ቤት አካባቢ ዛሬ የእነብርጋዲዬር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ቀጠሮ ነበር። ትንሽ ቆይቶ የተቃውሞ ድምፅ ሰማን፤ እስረኞች ይፈቱ የሚል። እናም ልንወጣ ስንል አስለቃሽ ጭስ ተተኮሰ እናም መውጣት አልቻልንም። እስከ ቤታችን ድረስ አይናችን እየተቃጠለ፤ አፋችንም ታፍኖ ነበር የደረስነው።" DAGI/TIKVAH-ETH/

POHTO: ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopua
#BAHIRDAR

የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በባህር ዳር ከተማ የተጣለው የ14 ቀን እንቅስቃሴ እገዳ ዛሬ 23/07/2012 ዓ/ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ ጀምሯል። የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን እገዳውን በማይተገብሩት ላይ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን አሳውቋል።

ምንጭ፦ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#BahirDar

በባሕር ዳር ከተማ ውሃ ተበክሏል እየተባለ የሚናፈሰው ወሬ #ሀሰት መሆኑን የባህር ዳር ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ለአብመድ ገልጿል፡፡

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የውሃ እና ፍሳሽ ባለሙያዎች በየዕለቱ በሁሉም ቦታዎች ማለትም (ታንከር ላይ ፣ መሥመር ላይና ቤት ለቤት በመዞር) የፊዚካል ፣ ባዮሎጂካል እንዲሁም የኬሚካል ናሙና ምርመራ ይደርጋሉ።

ዛሬ እና ትናንት በተደረገው የናሙና ምርመራ ምንም ችግር እንደሌለ መረጋገጡን የከተማው ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት አሳውቋል።

ዛሬ ህዳር 25/2013 ውሃ ተበክሏል በሚል ሥጋት ጥቆማ በተደረገባቸው የከተማዋ አካባቢዎች ናሙና ተወስዶ ምንም አይነት ችግር አለመኖሩ ተረጋግጧል።

የከተማው ውሃ በቀላሉ የሚበከል አለመሆኑ የተገለፀ ሲሆን በተለይም አጠራጣሪ በሆኑ አካባቢዎች የተጠናከረ ጥበቃ እየተደረገ ነው።

ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ/ም በኋላም የጥበቃ ሥራው መጠናከሩ ተገልጿል።

ሕዝቡ እውነቱን ተገንዝቦ 'ያለምንም መረበሽ' የእለት ተዕለት ተግባሩን እንዲከውን የከተማው ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት መልዕክት ተላልፏል። (AMMA)

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የ125ኛው ዓድዋ የድል በዓል እየተከበረ ይገኛል :

#Menelik_II_Square

125ኛው የዓድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በሚኒሊክ አደባባይ በተለያዩ ትዕይንቶች ታጅቦ እየተከበረ ይገኛል።

በበዓሉ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ ጀግኖች አርበኞች፣ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም የጉዞ አደዋ የዘንድሮ ተሳታፊዎች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡና የከተማዋ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

#MeskelSquare

የአድዋ የድል በዓል በመስቀል አደባባይ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በዓሉ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፥ የፌዴራል እና የክልል የስራ ሀላፊዎች፥ የጥንት አርበኞች፥ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ፥ ከተለያዩ የፊንፊኔ ዙሪያ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች የታደሙ 20 ሺህ የሚሆኑ ፈረሰኞች በተገኙበት እየተከበረ ይገኛል።

#Debremarkos

በአሁኑ ሰዓት የጎጃም ደብረማርቆስና አካባቢው ማህበረሰብ የአደዋን በዓል በንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ በመገኘት በማክበር ላይ ይገኛል።

#Bahirdar

በባህርዳር ከተማ 6ቱ ክፍለ ከተሞች በአንድነት 125ኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት እያከበሩ ነው።

በዓሉ የአማራ ክልል ርዕሰመስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር እና ሌሎች የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ይገኛል።

#Gondar

የአድዋ ድል በዓል በጎንደር ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በመከበር ላይ ይገኛል፡፡

በበዓሉ አባት አርበኞች፣ ወጣቶች፣ ልዩ ልዩ የጸጥታ አባላትና ከተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች የተወጣጡ ነዋሪዎች ታድመውበታል።

More : @tikvahethmagazine
#Bahirdar

ባህር ዳር ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።

የከተማው ኮሚኒኬሽን ቢሮ፥ "ከተማችን ሰላም ናት ወደመደበኛ እንቅስቃሴዋ ተመልሳለች" ነው ያለው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Bahirdar

በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር ከተማ ማታ ማታ የሚኒቀሳቀሱ ባጃጆች ቁጥር እንዲወሰን ተደረግ።

ይህ ውሳኔ የተላለፈው አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ወንጀል እንዳይከሰት ለመቆጣጠር ያመች ዘንድ እንደሆነ ተነግሯል።

እንደሀገር ሆነ እንደ ክልል የተከሰተውን የፀጥታ ሁኔታ በተገቢ መንገድ ለመምራት በባህር ዳር በህጋዊ መንገድ ተደራጅተው የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የባጃጅ ማህበራት ከከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ጽ/ቤት፣ ከፖሊስና መሰል የህግና የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር በሌሊት አገልግሎት የሚሰጡ ባጃጆች ተጠያቂነት ባለው አሰራር ታቅፈውና ለቁጥጥር እንዲያመች በቁጥር ተወስነው እንዲሰሩ መደረጉን የየማህበራቱ አስተባባሪዎች ተናግረዋል፡፡

በዚህ መሰረት ከስምንት የባጃጃ ማህበራት ውስጥ በስነ-ምግባር እና ለማህበረሰቡ ቅንና ታማኝ አገልግሎት ከሚሰጡ የባጃጅ አሽከርካሪዎች መካከል 120ዎችን በመመልመልና ከምሽቱ 3፡00 እስከ ንጋት 11፡00 ድረስ በሁሉም ቀበሌዎች እየተንቀሳቀሱ ከዛሬ ጀምሮ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል።

ይህ ለከተማው ሰላምና፣ ለማህበረሰቡ ደህንነት ሲባል የሚደረግ በመሆኑ የተመደቡ ባጃጆች ተጠያቂነት እንዲኖራቸው የማህበራቸውን ስምና አንፀባራቂ የደንብ ልብስ እንዲጠቀሙ፣ በዚያው ሰርጎ ገቦችን በመቆጣጠር በኩል ለሚደረገው ተግባር ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ መደረጉንም ገልፀዋል፡፡

ለዚህ ከተመደቡ ውጭ ማነኛውም ባጃጅ ከ3 ሰዓት ጀምሮ መንቀሳቀስ እንደሌለበትና ይህን ውሳኔ ተላልፎ የተገኘ የባጃጅ አሽከርካሪ ካለ በህግ ይጠየቃል ተብሏል።

የተመደቡት 120 ባጃጆች ያለምንም ዋጋ ጭማሪና ያለ አድሎ በሌለበት ሁኔታ እንዲሰሩ በሚሰጡት አገልግሎትም እጥረት ካለ እየተገመገመ እንደሚስተካከል ከ #ባህርዳር_ኮሚኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia