TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#GERD 🇪🇹 #ItsMyDam

- የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛው ዙር የውሃ ሙሌት እየተከናወነ ያለው ኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን እኤአ በ2015 በመሪዎቻቸው አማካኝነት በሱዳን ካርቱም በፈረሙት የመርህ ስምምነት መሰረት ነው።

- ኢትዮጵያ የመርህ ስምምነቱን መሰረት በማድረግ የግድቡን የግንባታ ደረጃ ተከትላ የውሃ ሙሌቱን ማከናወኗን ትቀጥላለች። በተያዘው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት የ18 ነጥብ 5 ቢሊዮን ኪውቢክ ሜትር ውሃ ሙሌት ተጀምሯል እንጂ አልተጠናቀቀም ብለዋል።

- የ2ኛው ዓመት የውሃ ሙሌት ነሃሴ መጨረሻ ላይ የጠናቀቃል።

- ታላቁ የኢትዮጰያ ህዳሴ ግድብ ባለፈው ዓመት ክረምት 4 ነጥብ 9 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ይዟል፤ በዘንድሮው ክረምት ደግሞ 13 ነጥብ 5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የሚይዝ ይሆናል።

#EngineerGedionAsfaw

@tikvahethiopia
#Update

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ መምከር ጀምሯል።

ስብሰባውን በቀጥታ በ United Nations የዩትዩብ ቻናል መከታተል ትችላላችሁ።

#ItsMyDam

@tikvahethiopia
#ItsMyDam

የግድባችን ሁለተኛው ዙር ውሃ ሙሌት እየተከናወነ ነው።

ግብፅ እና ሱዳን የግድባችንን ጉዳይ ወደተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ይዘውት ቢሄዱም ይህን ነው የሚባል ለውጥ አላመጡም ይልቁንም አብዛኛው የምክር ቤቱ ሀገራት ከሁለቱ ሀገራት በተቃራኒ የግድቡ ጉዳይ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት መፍትሄ እንዲፈለግለት የሚል አቋም አንፀባርቀዋል።

ከምክር ቤቱ ስብሰባ በኃላ ግብፆቹም ሆኑ ሱዳኖቹ አላረፉም፤ ከተለያዩ ሀገራት ጋር በግድቡ ጉዳይ ሃሳባቸውን ለማስረፅ እና ለማሳመን እየተነጋገሩ ነው።

ለአብነት ዛሬ የግብፁ ፕሬዜዳንት ከቻይናው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ስለግድቡ መክረዋል።

የግብፅ እና ሱዳን ሚዲያዎችም ቢሆኑ በየቀኑ ስለግድባችን ሳያነሱ አያልፉም። አሁንም ስለግድባችን የተሳሳቱ መረጃዎች ከማሰራጨት አልተቆጠቡም።

Egyptian Independent በተባለው ሚዲያ ብቻ ባለፉት 4 ቀናት ውስጥ ሰባት (7) የታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ ላይ ያተኮሩ ዘገባቸው ተሰርተዋል። በሌሎች ሚዲያዎች እንደነ Egypt Today ፣ Al-Ahram ፣ Daily News Egypt ላይ በርካታ ዘገባዎች ሲሰሩ ነበር።

ከፍተኛ መነጋገሪያ የነበረው ግን በ #Egypt_Today ላይ የወጣውና በሀገራችን ሚዲያዎች ተተርጉሞ የተሰራጨው ፕሬዜዳንት አል ሲ ሲ ሃያ ከሪማ ብሄራዊ ኮንፈረንስ ላይ ያደረጉት ንግግር ነው።

ንግግራቸው በሀገራችን ግዙፍ የሆኑ የሚዲያ ተቋማት ከአውድ ውጭ ተተርጉሞ/ሆን ተብሎ ብዙዎችን አሳስቷል። አንዳንዶች ግብፅ አቋም የቀየረች እንዲመስላቸው ሆኗል።

በእርግጥ የግብፁ ፕሬዜዳንት አል ሲ ሲ ምንድነው ያሉት ? ያንብቡ telegra.ph/Grand-Ethiopian-Renaissance-Dam-07-18

@tikvahethiopia
#ItsMyDam🇪🇹

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ሁለተኛው ዙር ሙሌት #ዛሬ_ለሊት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተሰምቷል።

የውሀው መጠን ግንባታው የደረሰበት ከፍታ ላይ ደርሶ ዛሬ ለሊት ሞልቶ ይፈሳል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህን መረጃ ይፋ ያደረገው "የሪፖርተር ጋዜጣ ድረገፅ" ሲሆን መረጃውን ከፕሮጀክቱ ስፍራ ማግኘቱን ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ItsMyDam🇪🇹 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ሁለተኛው ዙር ሙሌት #ዛሬ_ለሊት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተሰምቷል። የውሀው መጠን ግንባታው የደረሰበት ከፍታ ላይ ደርሶ ዛሬ ለሊት ሞልቶ ይፈሳል ተብሎ ይጠበቃል። ይህን መረጃ ይፋ ያደረገው "የሪፖርተር ጋዜጣ ድረገፅ" ሲሆን መረጃውን ከፕሮጀክቱ ስፍራ ማግኘቱን ገልጿል። @tikvahethiopia
#ItsMyDam🇪🇹

የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ በስፍራው ያሉ የግድቡ ሰራተኞች እየገለፁ ነው።

የውሀው መጠን ግንባታው የደረሰበት ከፍታ ላይ ደርሶ ሞልቶ ይፈሳል ተብሎ እየተጠበቀ ነው።

ሂደቱ ትላንት ለሊት የተጠበቀ ቢሆንም ሳይሆን ቀርቷል።

Photo Credit : Boni Kita (ከፕሮጀክቱ ስፍራ)

@tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ItsMyDam🇪🇹

የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ያስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት እና ስለሁለተኛው የግድቡ ሙሌት ለብሄራዊ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) የሰጡት ሙያዊ ማብራሪያ

Video : 133 MB (WIFI እንድትጠቀሙ እንመክራለን)

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ItsMyDam🇪🇹

ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሊት የመጀመሪያውን ሃይል ለማመንጨት የሚያስችለውን ውሃ ይዟል፡፡

ዛሬ ሃምሌ 12/ 2013 የውሃ ሙሊቱ ተጠናቆ ከግድቡ አናት ውሃው መፍሰስ ጀምሯል።

ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሊት በያዝነው ሀምሌና ነሃሴ ወር ላይ ለማድረግ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የዝናቡ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ከታሰበው ጊዜ ቀድሞ ውሃው ሊሞላ ችሏል።

በአመቱ የተከናወኑ ተግባራት የሁለተኛውን ዙር የውሃ ሙሊት ስኬታማ እንዲሆን እንዳስቻለው የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ በስፍራው ተገኝተው ተናግረዋል።

22 በሮች እና ትራሽ ክሊነሮች ፤ የስዊች ያርድ ፤ እንዲሁም የትራንስፎርመር ገጠማ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል ሚንስትሩ። አሁን ደግሞ የተርባይነሮች ገጠማ ስራ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ ፥ "በተለይ ዘንድሮ ግድቡን ለመገንባት የተኬደበት ፍጥንት የሚደነቅ ነው" ያሉ ሲሆን በቀጣይ ግድቡ እስኪጠናቀቅ በዚሁ ትጋት ስራው እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል፡፡ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ምንጭ፦ የውሃ ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#ItsMyDam🇪🇹

ዳይስፖራው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚያደርግበት ድረገፅ ይፋ ሆነ።

በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴው ግድብ ባሉበት ሆነው ድጋፍ የሚያሰባስብቡበት ድረገፅን መሰረት ያደረገ ፕላትፎርም ይፋ ሆኗል።

ይህ ፕላትፎርም www.mygerd.com ድረገፅ በመግባት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው።

በድረ-ገፁ አማካይነት የሚሰባሰበው ድጋፍ በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በዘመን ባንክ ለግድቡ ግንባታ ወደተከፈተው የውጭ ምንዛሬ አካውንት እንዲገባ የሚደረግ ሲሆን የሚውለውም ለታለመበት ዓላማ ብቻ ይሆናል ተብሏል።

ከዚህ ቀደም ለህዳሴው ግድብ ኢትዮጵያውያን በ8100 በኩል ድጋፍ ማድረግ የሚችሉበት አሰራር ተዘርግቶ በ3 የተለያዩ ዙሮች ከ252 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል፤ ግድቡ ግንባታው ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ በቦንድና በልገሳ ድጋፍ ተደርጓል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ItsMyDam🇪🇹 ዳይስፖራው ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ የሚያደርግበት ድረገፅ ይፋ ሆነ። በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴው ግድብ ባሉበት ሆነው ድጋፍ የሚያሰባስብቡበት ድረገፅን መሰረት ያደረገ ፕላትፎርም ይፋ ሆኗል። ይህ ፕላትፎርም www.mygerd.com ድረገፅ በመግባት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል ነው። በድረ-ገፁ አማካይነት የሚሰባሰበው ድጋፍ በብሔራዊ…
#ItsMyDam🇪🇹

ዛሬ ይፋ በተደረገው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማድረጊያ የድረገፅ ፕላትፎርም ዜጎች ድጋፍ ማድረግ ጀምረዋል።

Mygerd.com የተሰኘው ድጋፍ ማድረጊያ ድረገፅ ይፋ በተደረገ በደቂቃዎች ውስጥ 36 ሰዎች ባደረጉት ልገሳ ስለማድረጋቸው ታውቋል። በዚህም 1,899 የአሜሪካ ዶላር ሊሰበሰብ ችሏል።

አምስትሰዎች ለሌሎች በማስተዋወቅ ዘመቻውን ስለመቀላቀላቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወጣው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia