TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BidenHarris

በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዶናልድ ትረምፕን ያሸነፉት ጆ ባይደን ከወዲሁ የአስተዳደር ርክክብ ዝግጅት ፈጥነው ጀምረዋል።

በመጪው ጥር 20 (እ.አ.አ) ቃለ መሃላ ፈጽመው ሲረከቡ ቁልፍ የሆኑ የትረምፕ ፖሊሲዎችን ይቀለብሳሉ ተብሏል።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ ፥ ጆ ባይደን 'በጠባብ አጠቃላይ ድምጽ' ባሸነፉባቸው ክፍለ ግዛቶች ላይ የተፈጸሙ የድምጽ ቆጠራ መዛባቶች ሲፈተሹ ውጤቶቹ ተቀልብሰው አሸናፊ እኔ እሆናለሁ በማለት ክሶች መስርተዋል።

ተመራጩ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን እና ምክትላቸው ካማላ ሃሪስ ትናንት የሽግግር ዌብሳያታቸውን ከፍተዋል።

ፕሬዚዳንት ትረምፕ በምርጫው መሸነፋቸውን ለመቀበልም ሆነ ለጆ ባይደን ስልክ ደውለው ለማነጋገር ፈቃደኛ አልሆኑም ሲል #ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia