TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የተጠነቀቀ ይህን የከፋ ጊዜ ይሻገራል!

ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) የሩቅ ሀገር በሽታ ነው ሲባል እንዳልነበር ዓለምን አዳርሶ ዛሬ ሀገራችንን እያመሰ ነው።

በአዲስ አበባ አሁንም መደበኛ ህይወት የሚመራባቸው አካባቢዎች እንዳሉ ተመልክተናል። ይህ እጅግ ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍል ነው።

በአ/አ የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ቢገኝም አሁንም ከክልሎች ጋር 'የህዝብ ትራንስፖርት' አልቆመም ይህ ሁኔታ መላው የሀገሪቱን ህዝብ አደጋ ላይ እየጣለ ነው።

የክልል ከተሞች ላይ የሚታየው መዘንጋት ደግሞ ችግሩን የከፋ ሊያደርገው ይችላል። ጊዜው ሳይረፍድ መፍትሄ ቢፈልግ መልካም ነው።

የክልል ነዋሪዎች ጋር ቫይረሱ በስፋት ያለው አዲስ አበባ #ብቻ ነው እኛ ጋር አይደርስም በሚል የተሳሳተ አመለካከት ካለ አሁን መታረም አለበት።

የውጭ ሀገር ነው ሲባል የነበረው በሽታ ዛሬ ሀገራችን ፣ ሰፈራችን ደርሷል፤ #ካልተጠነቀቅን የእያንዳንዳችንን ቤት ማንኳኳቱ አይቀርም።

የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መከላከያ መንገዶች እጅግ በጣም ቀላል ሆነው ሳለ ለምን የማይገባ ዋጋ እንከፍላለን ?

• የእጆቻችንን ንፅህና እንጠብቅ! /መታጠብ/

• ቤት ውስጥ እንቀመጥ! /መቀመጥ/

• የስራችን ሁኔታ ከቤት የሚያስወጣና አስገዳጅ ጉዳዮች ኖረውን ከቤት ከወጣን የአፍንጫና አፍ መሸፈኛ እናድርግ! /መሸፈን/

• በሁሉም ቦታ አካላዊ ርቀት እንጠብቅ! /መራራቅ/

የኢትዮጵያ መንግስት የቫይረሱን ከፍተኛ ስርጭት ከግምት ውስጥ ሊያስገባና በህዝብ ትራስፖርቶች ላይ ያለውን ሁኔት ሳይውል ሳያድር መፍትሄ ሊፈልግለት ይገባል። ካልሆነ በሀገር ደረጃ የሚከፈለው ዋጋ ከፍተኛ ነው!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia