TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አሳዛኝ_ዜና! 5 የሜቆዶንያ የአእምሮ መርጃ ማዕከል ህመምተኞች በጎርፍ ተወስደው ህይወታቸው አለፈ። ዛሬ ጠዋት የሜቆዶንያ ማዕከል በሚገኘው መድሃኒዓለም ቤተክርስቲያን ፀበል ውስጥ ሲጠመቁ የነበሩ 5 ፀበልተኞቸ ደራሽ ውሃ መጥቶ ይዟቸው በመሄድ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሎል፡፡

ነብስ ይማር!

ምንጭ፦ ተሻገር ጣሰው
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና⬇️

በሶማሊያ የፑንትላንድ የንግድ ከተማ በሆነችው ቦሳሶ ውስጥ ሦስት #ኢትዮጵያዊያን #በአይሲስ ታጣቂዎች #ሲገደሉ ቢያንስ አንድ መቁሰሉ ተዘገበ።

ስለጥቃቱ በቀዳሚነት የወጡ ዘገባዎች እንዳመለከቱት ታጣቂዎቹ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ይኖሩበታል በሚባለው ሳንቶስ ተብሎ በሚጣራው የከተማዋ ክፍል ውስጥ ባገኟቸው አራት ኢትዮጵያዊያን ላይ #ተኩስ ከፍተው ነው ጥቃቱን የፈፀሙት።

አንድ ስማቸውን ያልጠቀሱ የአካባቢው ባለስልጣን ኢትዮጵያዊያኑ በተፈፀመባቸው ጥቃት መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ለቢቢሲ ሲያረጋግጡ፤ አፍቃሬ አይኤስ የሆነ ቡድንም በትዊተር ገጹ ላይ ስለጥቃቱ አስፍሯል።

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከተለያዩ ሃገራት የኤደን ባህረ ሰላጤን በትናንሽ ጀልባዎች በማቋረጥ ወደ የመንና የመካከለኛው ምሥራቅ ሃገራት በህገ ወጥ መንገድ ለመሻገር የሚፈልጉ ስደተኞች #የቦሳሶን የባህር በር ይጠቀማሉ።

በአካባቢውም በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንደሚገኙ ተገልጿል።

እነዚህ በጥቃቱ የሞቱትና የቆሰሉት ኢትዮጵያዊያንም በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች አማካይነት ባህሩን ተሻግረው በጦርነት ወደ የምትታመሰው #የመን ለመጓዝ በቦታው የነበሩ ስደተኞች እንደሆኑ ይታመናል።

አይሲስ ከቅርብ ወራት ወዲህ በጉልህ የሚታዩ በርካታ ጥቃቶችን በሶማሊያ ውስጥ እየፈፀመ ሲሆን በተለይ ደግሞ በፑንት ላንድ ግዛት ውስጥ የአይኤስ ቡደን ከሌሎች አካባቢዎች በበለጠ ሰፊ እንቅስቃሴ ያደርጋል ተብሎ ይታመናል።

ፑንትላንድ በሰሜን ሶማሊያ የምትገኝ ከፊል ራስ ገዝ የሆነች ግዛት ናት።

ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እውነታው ይሄ ነው‼️

"ኢትዮጲያ ዉስጥ በግልፅ ንገረን ካላችሁ፦ የመጨረሻ ኢትዮጲያ የምትባል ሀገር ያለችዉ #መከላከያ ዉስጥ ነዉ። ሌላዉማ ስለቀበሌዉ እና ስለቤተሰቡ #የሚያላዝን ህዝብ ነዉ ያለዉ ኢትዮጲያ ዉስጥ። ባለቤት ያጣች አሳዛኝ ሀገር ናት ኢትዮጲያ። ሁሉም #ስለመንደሩ የሚያወራ÷ ሀገር የሚባል ነገር ባለቤት ያጣባት #አሳዛኝ ሀገር ናት ኢትዮጲያ። ኢትዮጲያ ካለች÷ አሁን መከላከያ ዉስጥ ነዉ ያለችዉ። ወደዚ ዞር ስትሉ 'አካም' ትላላችሁ÷ ወደዚ ዞር ስትሉ 'ሰላም' ትላላችሁ÷ ወደዛ ስትዞሩ በሌላ ቋንቋ ትግባባላችሁ። ሌላ ቦታማ የለም÷ 'ዉጣልኝ እኮ ነዉ ያለዉ' እየያችሁ አይደለም?የኔ ካልሆንክ ዞር በል ነዉ ሌላ ቦታ ያለዉ። 'ኢትዮጲያዊ ነህ #ይገባሀል ኑር የሚል አይደለም። "

▪️ክቡር ጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ▪️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትላንት በለገጣፎ ለገዳዲ ምን ሆነ

ሰሞኑን በለገጣፎ ለገዳዲ የከተማው አስተዳደር ህገ ወጥ ናቸው ባላቸው የመኖሪያ ቤቶች ላይ የማፍረስ እርምጃ እየወሰደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህንን ተከትሎም ሚዲያዎች ወደአካባቢው በመሄድ ሁኔታው ሲዘግቡት ነበር።

በትላንትናው ዕለት የmereja.com ጋዜጠኛ እና የካሜራ ባለሞያ ሁኔታውን ለመዘገብ ወደ ለገጣፎ ለገዳዲ አምርተው #አሳዛኝ ክስተት ገጥሟቸው ተመልሰዋል።

የተፈጠረውን ክስተት በዝርዝር ለማስረዳት፦

Mereja.com ባልደረባ የሆኑ አንድ ጋዜጠኛ(ጋዜጠኛ ፋሲል) እና አንድ የካሜራ ባለሞያ በለገጣፎ ለገዳዲ የተወሰደውን እርምጃ ለመዘገብ ወደ አካባቢው ይሄዳሉ። ስራቸውን እንዳጠናቀቁም ፖሊስ ይመጣና መታወቂያ ይጠይቃቸዋል፤ ጋዜጠኛው እንዲሁም የካሜራ ባለሞያ በፖሊስ በተጠየቁት መሰረት መታወቂያቸውን ይሰጣሉ። ፖሊስም መታወቂያቸውን ኮፒ አድርጎ ይመልስላቸዋል። ከዚህ በኃላ ፖሊስ ስራውን ያለፍቃድ መስራት እንደማችሉ ይነግራቸዋል፤ ፖሊስ ረዘም ያለንግግር ከጋዜጠኛ ፋሲል ጋር ያደርጋል በመጨረሻም መግባባት ላይ ይደረስና የተያዘባቸው እቃ ተመልሶ እንዲሄዱ ይፈቀድላቸዋል።

ጋዜጠኛ ፋሲል እና የካሜራ ባለሞያው ጉዞያቸውን ወደአዲስ አበባ ለማድረግ ታክሲ ውስጥ ሊገቡ ሲሉ ቁጥራቸው ከ10-15 የሚደርሱ #ገጀራ እና #ዱላ የያዙ ወጣቶች በጋዜጠኛ ፋሲል ላይ ደብደባ መፈፀም ይጀምራሉ። ይህ በሚሆንበት ሰዓት የካሜራ ባለሞያው ራሱ ለማዳን ከአካባቢው ለመሰወር ችሏል።

አስገራሚው ነገር ወጣቶቹ በጋዜጠኛ ፋሲል ላይ #ድብደባ የፈፀሙት #ከፖሊስ_ጣቢያ ፊት ለፊት መሆኑ ነው። ፖሊስ በመሃል ገብቶ ከመገላገል ውጭ፤ ወጣቶቹ ለምን ድብደባ እንደፈፁሙ እንኳን ይዞ #አልጠየቃቸውም። የተደራጁት ወጣቶች ከአካባቢው ከሄዱ በኃላ ጋዜጠኛ #ፋሲል በግለሰብ መኪና ወደጤና ተቋም እንዲሄድ ይደረጋል በወቅቱ ምንም አይነት የፀጥታ ሀይል አብሮት አልሄደም።

በጋዜጠኛ ፋሲል ላይ በደረሰው ድብደባ በጭንቅላቱ ላይ 2 ቦታ የመሰንጠቅ አደጋ ደርሷል እዲሁም ከፍተኛ ደም ፈሷል፤ ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታልም ሪፈር ተብሎ የሄደ ሲሆን የደረሰበት አደጋ ከፍተኛ ቢሆንም በቤቱ ተኝቶ ህክምናውን መከታተል እንደሚችል ተነግሮ ወደቤቱ ተመልሷል።

ምንጭ፦ ወ/ሮ ፍሬዘር ነጋሽ(የmerej.com ስራ አስኪያጅ) - ለTIKVAH-ETH

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና በምሥራቅ አፍሪካ ሃገራት ውስጥ ስኬታማውና በኢትዮጵያ ገበያም ለመሳተፍ ፍላጎት ያሳየው ግዙፉ የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ቦብ ኮሊሞር ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ድርጅታቸው አስታደቀ። ሳፋሪኮም የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ዜና እረፍት ይፋ ባደረገበት መግለጫው ላይ እንዳመለከተው፤ ቦብ ኮሊሞር በ61 ዓመት እድሜያቸው በካንሰር ምክንያት ዛሬ ጠዋት ቤታቸው ውስጥ ህይወታቸው ማለፉን ገልጿል።

Via #BBC
🗞ቀን ሰኔ 24/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና

በሱዳን በተካሂደ የተቃውሞ ሰልፍ የሰባት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ከ180 በላይ በሚሆኑት ላይ ደግሞ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን የሀገሪቱ ዜና አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ከባለፈው ሚያዝያ ወር ጀምሮ በኃይል ከሥልጣን የወረዱት የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኦማር አልበሽር ዘመን ወዲህ ሱዳን መረጋጋት ተስኗታል። ትናንት በመዲናዋ በተካሄደ ሰልፍም በሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፤ ወታደራዊ የሽግግር መንግሥቱ ለጥቃቱ ራሳቸውን ‹የነፃነትና የለውጥ ኃይል› ብለው የሚጠሩ ብድኖችን እና ሰርጎ ገቦችን ወንጅሏል፡፡ ተኩስ ከፍተዋል ያላቸውን ሰርጎ ገቦች ማሠሩንም አስታውቋል፡፡

Via ቢቢሲ
🗞ቀን ሰኔ 24/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና

የአስራ ስምንት አመት እድሜ ያለው ሰለሞን ተካ እስራኤል ውስጥ ሐይፋ በሚባለው አካባቢ ፖሊስ በጥይት ደብድቦ የገደለው ሲሆን በዛሬው ዕለትም ስርአተ ቀብሩ እንደሚፈፀም ጀሩሳሌም ፖስት ዘግቧል።

በትናንትናው እለት በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አሟሟቱን በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል።

ሰልፈኞቹ በፖሊሶች ላይ ድንጋይ በመወርወርና እሳት በማቀጣጠል ተቃውሟቸውን የገለፁ ሲሆን በዚህም ሶስት ፖሊሶች ተጎድተዋል። ፖሊስ በበኩሉ አፀፋዊ ምላሽ የሰጠ ሲሆን በዚህ ቁጥራቸው ትንሽ የማይባሉ ሰልፈኞች ተጎድተዋል።

ሰለሞንን ገደለ የተባለው ፖሊስ በነፍስ ግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር እንደዋለም ሀሬትዝ ዘግቧል።

Via #bbc
🗞ቀን ሰኔ 25/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና

በህንድ ሙምባይ የወሰን ግንብ ተደርምሶ የ13 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ አደጋው የደረሰው በህንድ የንግድ ከተማ ሙምባይ በጣለ ከባድ ዝናብ ነው፤ በዚህም ቢያንስ የ13 ሰዎች ሕይወት እንዳለፈና መኖሪያዎችም እንደፈራረሱ ታውቋል፡፡ ከአደጋው በርካታ ሰዎችን ማትረፍ ተችሏል፤ የነፍስ አድን ሠራተኞች ሰዎችን ከጉዳት የማትረፍ ሥራቸውን እንደቀጠሉም ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡ በአደጋው የባቡር እንቅስቃሴ እና የአየር በረራ ተቋርጧል፡፡ ሀገሪቱም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማወጅ እንደምትገደድ ባለስልጣናቱ እየገለጹ ነው፡፡

Via ሲ ጂ ቲ ኤን
🗞ቀን ሰኔ 25/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና

ዛሬ ማለዳ በሊቢያ የስደተኞች እስር ቤት ላይ በተፈጸመ የአየር ድብደባ በትንሹ 44 ሰዎች #መገደላቸውን የአገሪቱ መንግሥት አስታወቀ። በትሪፖሊ ከተማ ታጁራ በተባለ አካባቢ በሚገኘው የስደተኞች እስር ቤት ላይ ባነጣጠረው የአየር ድብደባ 130 በላይ ስደተኞች መቁሰላቸውን በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፈው የሊቢያ መንግሥት የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በትንሹ 6,000 #ኢትዮጵያውያን፣ ኤርትራውያን፣ ሶማሌያውያን፣ ሱዳናውያን እና የሌሎች የአፍሪካ አገራት ዜጎች በሊቢያ ታጣቂዎች ቁጥጥር ሥር በሚገኙት እስር ቤቶች ታጉረው ይገኛሉ። አብዛኞቹ ስደተኞች ወደ አውሮፓ ለመሻገር ሲሞክሩ የተያዙት የአውሮፓ ኅብረት በገንዘብ በሚደግፋቸው እና ባሰለጠናቸው የባሕር በር ጠባቂዎች ነው።

Via #DW
🗞ቀን ሰኔ 26/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አሳዛኝ_ዜና

በሶማሊያ በአንድ ሆቴል ላይ በተሰነዘረ ጥቃት ታዋቂ ጋዜጠኛን ጨምሮ 26 ሰዎች ሞቱ። በደቡባዊ ሶማሊያ በተሰነዘረ ጥቃት ከሞቱት 26 ሰዎች መካከል ታዋቂ ጋዜጠኛ ፣በርካታ የውጪ ዜጎች እንደሚገኙበት ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ከጥቃት አድራሾቹ መካከል አንድ አጥፍቶ ጠፊ ፈንጂዎችን የጫነ ተሸከርካሪ በኪስማዩ ወደብ ወደ ሚገኘው አሳሴይ ሆቴል በሃይል ጭኖ የገባ ሲሆን ሌላ ታጣቂም ወደ ህንፃው በመግባት ጉዳት አድርሰዋል፡፡

የ43 አመቷ ጋዜጠኛ ሁዳን ናላሂ እና ባለቤቷ ፋሪድ ከሟቾቹ መካከል ይገኙበታል፡፡ አልሻባብ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ሲሆን እኤአ በ2012 ከኪስማዩ ተገዶ ከወጣ በኋላ የፈፀመው አስከፊ ጥቃት ተብሏል፡፡

የሃገሪቱ ባለስልጣናት እንዳሉት የአካባቢው ፖለቲከኞች ፣ሶስት ኬንያውያን፣ሶስት ታንዛኒያውያን ፣ሁለት አሜሪካኖችና አንድ ብሪታኒያዊ በጥቃቱ ህይወታቸው አልፏል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia