TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከተሽከርካሪ ነፃ ቀን!

“ጤናማ የአኗኗር ዜይቤ ለጤናማ ሕይወት” በሚል መሪ ቃል መንገዶችን ከተሽከርካሪ ፍሰት #ነፃ በማድረግ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማክበር ማቀዱን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችንና አጋላጭ መንስኤዎቻቸውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በማሰብ መርሃ ግብሩ እንዳዘጋጀ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡

ፕሮግራሙ ለጊዜው #በአዲስ_አበባ ከተማ ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን በሂደት ወደ ሌሎች የአገሪቱ ትላልቅ ከተሞች ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡

በወጣው መርሃ ግብር መሰረት ከተሽከርካሪ ነፃ በሚሆኑ የተመረጡ መንገዶች ላይ የአካል እንቅስቃሴዎች፣ ተላለፊ ላልሆኑ በሽታዎች ነፃ ምርመራዎች እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በሚል ይከናወናሉ፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ማራቶን ሞተርስ ኢንጀኒነሪንግ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ያስገነባው #የሃንዳይ_መኪና የመገጣጠሚያ ፋብሪካ ዛሬ ተመረቀ። ግማሽ ቢሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ወጪ የተደረገበት የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካው #በአዲስ_አበባ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ቱሉ ዲምቱ አካባቢ ነው የተገነባው።

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia