TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በሚገኙ ሁለት ወረዳዎች በመስጊዶች ላይ የደረሱ ጥቃቶችን አጥብቆ #እንደሚያወግዝ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ገለፀ፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተጠርጣሪዎቹ ከእስር እየተለቀቁ ነው‼️

የድሬደዋ አስተዳደር በቅርቡ በከተማው በተካሄደው ተቃውሞ እና ሁከት ጋር በተያያዘ #ጠረጠርኳቸው በሚል በቁጥጥር ስር ካዋላቸው ከሦስት መቶ በላይ ሰዎች የአብዛኞቹን ክስ በማቋረጥ በነፃ እየለቀቀ ይገኛል። ከቀናት አስር በኃላ በቂ ማስረጃ ባለመኖሩ የተለቀቁ ተጠርጣሪዎችና ቤተሰቦች እንዲሁም ወዳጆች በእምባ ተራጭተዋል፡፡ በከተማው ለቀናት የተከሰተውን ተቃውሞ ተከትሎ የፀጥታ ሀይሉ በወሰደው ሰፊ እርምጃ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ተጠርጣሪዎችን አፍሶ በመያዝ ከአስራ አምስት ቀናት በላይ በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው ሲመረመር ቆይቷል፡፡ ከነዚህ ተጠርጣሪዎች ሁለት መቶ አስራ ስምንት የሚሆኑትን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እና ፖሊስ ውሰኔ ክሳቸው ተቋርጦ በነፃ እንዲለቀቁ ተደርጓል፡፡

ከሳምንት በፊት በሀላፊነት የተሾሙት የአስተዳደር ፖሊስ ኮምሽን ኮምሽነር ኮማንደር አለሙ መርጋ ተጠርጣሪዎቹ ስለተለቀቁበት ምክንያት አስረድተዋል፡፡

ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ተጠርጣሪዎችን በመልቀቅ ላይ የሚገኙት ጠቅላይ ዐቃቤ ህግና ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ከመልቀቃቸው በፊት ከተጠርጣሪዎች ፣ ከቤተሰብና በነፃ ጥብቅና ቆመው ከነበሩ የህግ ባለሞያዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ኮምሽነሩ ስለውይይቱ ዓላማ ተናግረዋል፡፡ በተለያዩ ቀናት በተካሄደው በዚህ ውይይት በከተማው የተፈጠረውን ሁከት ተከትሎ በጅምላ ተይዘው የቆዩ ተጠርጣሪዎች ከድርጊቱ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት ሳይኖር ጭምር መሆኑነንና፣ በምርመራ ሂደትም ከመርማሪዎች ከብቃት ጋር የተያያዙ ችግሮች እንደነበሩ ተነስተዋል፡፡ ወጣቶቹም #በሰላማዊ መንገድ ትግላችንን እንቐጥላለል ብለዋል፡፡

ከህብረተሰቡ ለተነሱት ጉዳዮች በፖሊስ እና ዐቃቤ ህግ በኩል ተወስደው የሚታረሙ መሆኑ ተገልፇል፡፡ በሌላ በኩል ከዚሁ ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው ፍ/ቤት ቀርበው ግዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ከነበሩና ዛሬ ፍርድ ቤት ከሚቀርቡ ዘጠና ተጠርጣሪዎች አብዛኞቹን ክስ በማቋረጥ መልቀቃቸው ለፍ/ቤቱ ተገልፃል፡፡

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ታንዛኒያ ሰሞኑን 1 ሺህ 900 ኢትዮጵያዊያን ስደተኛ እስረኞችን #ለመልቀቅ ተስማምታለች፡፡ እስረኞቹ የሚለቀቁት በዳሬሰላም የኢትዮጵያ ኢምባሲ ከታንዛኒያ መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ባደረገው ስምምነት መሠረት መሆኑን የኬንያው ዴይሊ ኔሽን አስነብቧል፡፡ ስደተኞቹ በምን ወንጀል እንደታሰሩ ባይገለጽም በርካታ ስደተኞች በየጊዜው በሕገ ወጥ መንገድ በታንዛኒያ በኩል አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊሻገሩ ሲሉ እንደሚያዙ ተደጋግሞ ተዘግቧል፡፡

Via wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
“የህዳሴ ግድብን #ለማጠናቀቅ ተጨማሪ ማራዘሚያ ጊዜ ሊኖር አይገባም” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር #ደመቀ_መኮንን
.
.
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተያዘው የጊዜ መርሃ-ግብር ለማጠናቀቅ ርብርብ መደረግ እንደሚገባ የግድቡ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሄራዊ ምክር ቤት ሰብሳቢ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።

በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞለት የነበረው ግድቡ ስምንት ዓመታት አለመጠናቀቁን የተናገሩት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህም በኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) መሰራት የነበረበት የግድቡ ኤሌክትሮ ሜካኒካልና ተያያዥ ተግባራት አፈፃፀም #በመጓተቱ ነው ብለዋል።

በዚህም የተነሳ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ ተጨማሪ አራት ዓመታት አስፈልጓል፤ ይሁንና አሁን ላይ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ፕሮጀክቱን በተያዘው የጊዜ ገደብ በጥራትና በብቃት ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ክትትል ያደርጋል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በመንግስትና በኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) መካከል እርቅ ለማውረድ የተቋቋመው የቴክኒክ ኮሚቴ የፊታችን ረቡዕ ወደተለያዩ የኦሮሚያ ዞኖች እንደሚሰማራ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡ ኮሚቴው ወደ ወለጋ ዞኖች፣ ጉጂ ዞኖችና ቦረና ዞን፣ ሰሜን ሸዋ፣ ኢሉ አባቦራና ፈንታሌ ዞኖች እንደሚሰማራ ገልጿል፡፡ ኮሚቴው ከሁለቱም አካላት ጋር ውይይት ማድረጉንና ከዚህ ቀደም ተወስኖ የነበረው ቀነ ገደብ ላይ ተጨማሪ 10 ቀናት መጨመሩን የቀድሞ የቱለማ አባገዳ #በየነ_ሰንበቶ ገልጸዋል፡፡

ምንጭ:- OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ🔝

በበደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት #በሃዋሳ ከተማ የታክስ ንቅናቄ መድረክ የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ #አዳነች_አቤቤ በተገኙበት በይፋ ተከፈተ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የተሰየሙት የእርቀ ሰላም ኮሚሽን አባላት ዛሬ ትውውቅ አድርገዋል። በትውውቅ ፕሮግራሙ ለእርቀ ሰላም ኮሚሽን ተልዕኮ ስኬት መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ገልፀዋል።

ምንጭ:- ም/ጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ክልል ፖሊስ‼️

በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ 43 ክላሽ ሸንኮቭ የጦር መሳሪያና 1 ሺህ 300 ጥይቶች በቁጥ ጥር ስር ማዋሉን #የአማራ_ክልል_ፖሊስ አስታወቀ።

#የጦር_መሳሪያዎቹን ከጋምቤላ ወደ አማራ ክልል ጎንደር ከተማ በኤፍ ኤስ አር የጭነት ተሽከርካሪ በማስገባት ላይ እያለ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን፥ የመኪናው አሽከርካሪም በቁጥጥር ሥር መዋሉን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን
ገልጿል።

በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ የጦር መሳሪያዎች ላይ ተጨማሪ የምርመራ ሥራ እያከናወነ መሆኑንም ነው ኮሚሽኑ የገለፀው።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መካነሰላም🔝

ሰሞኑን በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ #የተቃጠሉ መስጊዶችን መልሶ ለመገንባት ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር በእስቴ መካነሰላም ከተማ ተካሂዷል።

Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia