TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተሸለመ🔝

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ እና #አመልድ የሀገሪቱን #ጥራት ሽልማት አሸነፉ፡፡ የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በጥራት መስፈርት ካወዳደራቸው 52 ተቋማት መካከል 40ዎቹን በተለያየ ደረጃ እንዲሸለሙ አድርጓል፡፡ ውድድሩ አገልግሎት ሰጪዎችን፣ የግንባታ ድርጅቶችን፣ አምራችና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ያካተተ ነው፡፡

በውድድሩ መሰረት የአንደኛ ደረጃ ዋንጫ አሸናፊ የሆኑት ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ አማራ መልሶ ማቋቋም ድርጅት እና ሀረር ቢራ አክሲዮን ማህበር ናቸው፡፡

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ ውድድር ለሦስት ተከታታይ ጊዜ አሸናፊ በመሆኑ የልዩ ዋንጫም ተሸላሚ ሆኗል፡፡

የኢትዮጵያ ምርቶች እና አገልግሎቶች በዓለም ገበያ ተቀባይነትን አግኝተው ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በጥራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ለነገ የማይባል ጉዳይ መሆኑን ክብርት ፕሬዝደንት ገልፀዋል፡፡

ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ያቀረባቸውን የጥራት ውድድር አሸናፊዎች ሸልመዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia